-
ቤተሰባችሁን ማስተዳደር የምትችሉት እንዴት ነው?ለቤተሰብ ደስታ ቁልፉ ምንድን ነው?
-
-
16, 17. (ሀ) እስራኤላውያን ከአንዳንድ በሽታዎች እንዲጠበቁ የረዳቸው የትኛው የይሖዋ ሕግ ነው? (ለ) ከዘዳግም 23:12, 13 በስተጀርባ ያለው መሠረታዊ ሥርዓት በሁሉም ቤተሰቦች ውስጥ ሥራ ላይ ሊውል የሚችለው እንዴት ነው?
16 አንድ ሌላ ምሳሌ ደግሞ እንመልከት። ወደ 3,500 ከሚጠጉ ዓመታት በፊት አምላክ ለእስራኤል ሕዝብ የአምልኮ ሥርዓታቸውንና በተወሰነ ደረጃ ደግሞ የዕለት ተዕለት ኑሯቸውን ማደራጀት እንዲችሉ ሕግ ሰጥቷቸው ነበር። ይህ ሕግ አንዳንድ መሠረታዊ የሆኑ የንጽሕና አጠባበቅ መመሪያዎችን የያዘ ስለነበር ሕዝቡ ከበሽታ እንዲጠበቁ ረድቷቸዋል። ከእነዚህ ሕጎች አንዱ እንዴት መጸዳዳት እንዳለባቸው የሚገልጽ ነበር፤ በሕጉ መሠረት ሰዎች የሚኖሩበት አካባቢ እንዳይበከል ከሰፈሩ ውጪ ባለ ሥፍራ ጉድጓድ ቆፍረው መጸዳዳትና አፈሩን መልሰው መሸፈን ነበረባቸው። (ዘዳግም 23:12, 13) ይህ ጥንታዊ ሕግ በዛሬው ጊዜም የሚሠራ ጥሩ ምክር ነው። በአሁኑ ዘመንም እንኳ ሰዎች ይህን ሥርዓት ባለመከተላቸው ይታመማሉ፣ ከዚያም አልፎ ይሞታሉ።a
-
-
ቤተሰባችሁን ማስተዳደር የምትችሉት እንዴት ነው?ለቤተሰብ ደስታ ቁልፉ ምንድን ነው?
-
-
a የዓለም የጤና ድርጅት ለብዙ ጨቅላ ሕፃናት ሞት ምክንያት የሆነውንና በጣም ተስፋፍቶ የሚገኘውን የተቅማጥ በሽታ ማስወገድ የሚቻልበትን መንገድ በተመለከተ ባወጣው መመሪያ መጽሐፍ ላይ እንዲህ ብሏል:- “መጸዳጃ ቤት ከሌለ ከቤት ራቅ ባለና ልጆች በማይጫወቱበት እንዲሁም ደግሞ ውኃ ከምትቀዱበት ቦታ ቢያንስ 10 ሜትር ያህል ርቀት ላይ በሚገኝ ሥፍራ ከተጸዳዳችሁ በኋላ ዓይነ ምድሩን በአፈር ሸፍኑት።”
-