-
“ምግባረ መልካም ሴት”መጠበቂያ ግንብ—2012 | ጥቅምት 1
-
-
ሩት ቤት ስትደርስ ኑኃሚን “ልጄ፣ አንቺ ማነሽ?” (NW) አለቻት። ምናልባትም ኑኃሚን እንዲህ ብላ የጠየቀቻት በደንብ ስላልነጋ ማንነቷን መለየት አቅቷት ሊሆን ይችላል፤ በሌላ በኩል ደግሞ ኑኃሚን፣ ሩት የሚያገባት ሰው አግኝታለች ወይስ እንደ ቀድሞዋ ብቸኛ መበለት ናት የሚለውን ማወቅ ፈልጋ ይሆናል። ሩትም ከቦዔዝ ጋር የተነጋገሩትን በሙሉ ወዲያው ለአማቷ ነገረቻት። በተጨማሪም ቦዔዝ ለኑኃሚን የላከላትን ገብስ ሰጠቻት።d—ሩት 3:16, 17
-
-
“ምግባረ መልካም ሴት”መጠበቂያ ግንብ—2012 | ጥቅምት 1
-
-
d ቦዔዝ ለሩት ስድስት መስፈሪያ (መለኪያው አልተገለጸም) ገብስ መስጠቱ፣ ከስድስት የሥራ ቀናት በኋላ የሰንበት እረፍት እንደሚኖር ሁሉ ሩትም በመበለትነት ያሳለፈችው የልፋት ዘመን አብቅቶ ባል ማግባትና ኑሮ መመሥረት የሚያመጣውን እረፍት የምታገኝበት ጊዜ እንደቀረበ የሚያመለክት ሊሆን ይችላል። በሌላ በኩል ደግሞ ስድስት መስፈሪያ ገብስ (ምናልባትም በአካፋ እየዛቀ) የሰጣት ሩት ልትሸከም የምትችለው ይህን ያህል ብቻ ስለሆነ ሊሆን ይችላል።
-