-
“ምግባረ መልካም ሴት”በእምነታቸው ምሰሏቸው
-
-
1, 2. (ሀ) ሩት ምን እየሠራች ነበር? (ለ) ሩት የአምላክን ሕግና ሕዝቦቹን በተመለከተ ምን መልካም ነገር መገንዘብ ችላለች?
ሩት ቀኑን ሙሉ ስትሰበስብ ውላ በቆለለችው የገብስ ነዶ አጠገብ በርከክ ብላለች። ቀኑ ለዓይን ያዝ ማድረግ ጀምሯል፤ በቤተልሔም ዙሪያ ባሉት ማሳዎች ላይ ሲሠሩ የዋሉ በርካታ ሠራተኞች በአቅራቢያው ባለው ኮረብታ ላይ ወደምትገኘው ትንሽ ከተማ ማዝገም ጀምረዋል። ሩት ከማለዳ ጀምራ ቀኑን ሙሉ ያለ እረፍት ስትለፋ ስለዋለች ሰውነቷ እንደዛለ ጥርጥር የለውም። ያም ሆኖ፣ ገና ሥራዋን አልጨረሰችም፤ እህሉን ከገለባው ለመለየት በበትር መውቃት ጀመረች። ሥራው አድካሚ ቢሆንም ካሰበችው በላይ አስደሳች ቀን አሳልፋለች።
-
-
“ምግባረ መልካም ሴት”በእምነታቸው ምሰሏቸው
-
-
5, 6. (ሀ) ሩት በቦዔዝ እርሻ ውስጥ በቃረመችበት በመጀመሪያው ቀን ምን ያህል ተሳክቶላት ነበር? (ለ) ኑኃሚን ሩትን ስታያት ምን ተሰማት?
5 ሩት የቃረመችውን ገብስ ከወቃች በኋላ ስትሰፍረው አንድ የኢፍ መስፈሪያ ወይም 22 ሊትር ያህል ሆነ። ምናልባትም የሰበሰበችው እህል 14 ኪሎ ግራም ገደማ ሳይሆን አይቀርም! እህሉን በጨርቅ ቋጥራ በጭንቅላቷ በመሸከም ወደ ቤቷ ማዝገም ጀመረች፤ ወደ ቤተልሔም ስትደርስ ጨለምለም ብሎ ነበር።—ሩት 2:17
-