የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • አስተዋይነት የተንጸባረቀበት እርምጃ ወስዳለች
    በእምነታቸው ምሰሏቸው
    • ቆንጆዋ አቢግያ

      ምዕራፍ ዘጠኝ

      አስተዋይነት የተንጸባረቀበት እርምጃ ወስዳለች

      1-3. (ሀ) በአቢግያ ቤተሰብ ላይ አደጋ እንዲያንዣብብ ምክንያት የሆነው ምንድን ነው? (ለ) ግሩም ባሕርይ ያላትን ይህችን ሴት በተመለከተ የትኞቹን ጥያቄዎች እንመረምራለን?

      አቢግያ ፊቷ የቆመው ወጣት እንደተደናገጠ ከሁኔታው ማስተዋል ችላለች። ወጣቱ በጣም ተረብሿል፤ ደግሞም የተረበሸበት በቂ ምክንያት አለው። በቤተሰቡ ላይ ከባድ አደጋ አንዣቧል። በዚህ ወቅት፣ በአቢግያ ባል በናባል ቤተሰብ ውስጥ የሚገኙትን ወንዶች በሙሉ ጠራርገው ለማጥፋት ቆርጠው የተነሱ 400 የሚያህሉ ጦረኞች ወደ ናባል ቤት እየገሰገሱ ነበር። ለመሆኑ ይህን እርምጃ ለመውሰድ ያነሳሳቸው ምንድን ነው?

      2 ለዚህ ሁሉ ችግር መንስኤው ናባል ነበር። ናባል እንደ ልማዱ ሌሎችን የሚያዋርድና ርኅራኄ የጎደለው ድርጊት ፈጽሟል። በዚህ ወቅት የተሳደበው ግን ፈጽሞ ሊዳፈረው የማይገባውን ሰው ይኸውም የሠለጠኑና ታማኝ የሆኑ ተዋጊዎች ያሉትን ተወዳጅ መሪ ነው። በመሆኑም ከናባል ወጣት ሠራተኞች አንዱ፣ ምናልባትም ከእረኞቹ መካከል ሳይሆን አይቀርም አቢግያ እነሱን ለማዳን አንድ መላ እንደምትፈጥር ተስፋ በማድረግ ወደ እሷ መጣ። ይሁንና አንዲት ሴት አንድን ሠራዊት እንዴት መመከት ትችላለች?

      አንዲት ሴት አንድን ሠራዊት እንዴት መመከት ትችላለች?

  • አስተዋይነት የተንጸባረቀበት እርምጃ ወስዳለች
    በእምነታቸው ምሰሏቸው
    • “የስድብ ናዳ አወረደባቸው”

      8. ናባል የሰደበው ማንን ነበር? ይህን ማድረጉስ የሞኝነት ተግባር ነበር የምንለው ለምንድን ነው?

      8 ናባል በዚህ ወቅት የወሰደው እርምጃ የአቢግያ ሕይወት ይበልጥ አስቸጋሪ እንዲሆን የሚያደርግ ነበር። ናባል የሰደበው ሌላን ሰው ሳይሆን ዳዊትን ነው! ዳዊት ደግሞ ሳኦልን ተክቶ ንጉሥ እንዲሆን አምላክ የመረጠውና ነቢዩ ሳሙኤል የቀባው ታማኝ የይሖዋ አገልጋይ ነበር። (1 ሳሙ. 16:1, 2, 11-13) በወቅቱ ዳዊት በቅንዓት ተነሳስቶ ሊገድለው ያሳድደው ከነበረው ከንጉሥ ሳኦል በመሸሽ ከ600 ታማኝ ተዋጊዎቹ ጋር በምድረ በዳ ይኖር ነበር።

አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
ውጣ
ግባ
  • አማርኛ
  • አጋራ
  • የግል ምርጫዎች
  • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
  • የአጠቃቀም ውል
  • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
  • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
  • JW.ORG
  • ግባ
አጋራ