-
አስተዋይነት የተንጸባረቀበት እርምጃ ወስዳለችመጠበቂያ ግንብ—2009 | ሐምሌ 1
-
-
ታታሪ ሠራተኞች የነበሩት የዳዊት ወታደሮች ከእረኞቹ ጋር የነበራቸው ግንኙነት ምን ይመስላል? የዳዊት ወታደሮች በፈለጉት ጊዜ ከናባል መንጋ በጎችን መዝረፍ ይችሉ ነበር፤ እነሱ ግን እንዲህ አላደረጉም። ከዚህ በተቃራኒ እንደ አጥር በመሆን የናባልን መንጎችና እረኞች ከጥቃት ጠብቀዋቸዋል። (1 ሳሙኤል 25:15, 16) በጎችም ሆነ የሚጠብቋቸው እረኞች ለአደጋ የተጋለጡ ናቸው። በዚያ ዘመን አውሬዎች በአካባቢው በብዛት ይገኙ ነበር። ከዚህም በተጨማሪ ቦታው ለእስራኤል ደቡባዊ ድንበር ቅርብ በመሆኑ ከባዕድ አገር የሚመጡ ወንበዴዎችና ዘራፊዎች ብዙ ጊዜ ጥቃት ይሰነዝሩ ነበር።b
-
-
አስተዋይነት የተንጸባረቀበት እርምጃ ወስዳለችመጠበቂያ ግንብ—2009 | ሐምሌ 1
-
-
b ዳዊት በአካባቢው የነበሩትን ባለርስቶችና መንጎቻቸውን ከጥቃት መጠበቅን ይሖዋ አምላክን እንደማገልገል አድርጎ ሳይቆጥረው አልቀረም። በዚያ ዘመን የአብርሃም፣ የይስሐቅና የያዕቆብ ዝርያዎች በዚያ አካባቢ እንዲኖሩ የይሖዋ ዓላማ ነበር። በመሆኑም ይህንን አካባቢ ከባዕድ አገር ከመጡ ወራሪዎችና ዘራፊዎች ጥቃት መጠበቅ ለይሖዋ የሚቀርብ ቅዱስ አገልግሎት እንደሆነ ተደርጎ ይታይ ነበር።
-