-
ለአምላክ የልቧን አውጥታ ነገረችውበእምነታቸው ምሰሏቸው
-
-
15, 16. (ሀ) ሐና የልቧን አውጥታ ለይሖዋ መንገሯና በማደሪያ ድንኳኑ አምልኮዋን ማቅረቧ ምን ውጤት አስገኘላት? (ለ) እኛም አፍራሽ ከሆኑ ስሜቶች ጋር በምንታገልበት ጊዜ ሐና የተወችውን ምሳሌ መከተል የምንችለው እንዴት ነው?
15 ሐና ለይሖዋ የልቧን አውጥታ መናገሯና በማደሪያ ድንኳኑ ለእሱ አምልኮ ማቅረቧ ምን ውጤት አስገኘ? ዘገባው “መንገዷን ሄደች፤ ምግብም በላች፤ ከዚያም በኋላ በፊቷ ላይ ሐዘን አልታየም” ይላል። (1 ሳሙ. 1:18) ሐና ጭንቀቷ ቀሎላት ነበር። እንደ ከባድ ሸክም ሆኖ ስሜቷን የደቆሳትን ነገር ከእሷ ይልቅ ኃያል በሆነው ሰማያዊ አባቷ ጫንቃ ላይ የጣለችው ያህል ነበር። (መዝሙር 55:22ን አንብብ።) ለይሖዋ ከአቅሙ በላይ የሚሆንበት ችግር ሊኖር ይችላል? በጭራሽ! ያኔም ሆነ አሁን ወይም ደግሞ ወደፊት ሊኖር አይችልም!
16 እኛም አንድ ነገር ሲያስጨንቀን፣ ከአቅማችን በላይ እንደሆነ ሲሰማን ወይም በሐዘን ስንዋጥ የሐናን ምሳሌ በመከተል መጽሐፍ ቅዱስ ‘ጸሎት ሰሚ’ በማለት ለሚጠራው አምላክ የልባችንን አውጥተን መንገራችን መልካም ነው። (መዝ. 65:2) በእምነት እንዲህ ካደረግን እኛም ሐዘናችን ተወግዶ ‘ከማሰብ ችሎታ ሁሉ በላይ በሆነው የአምላክ ሰላም’ እንደተተካ ሊሰማን ይችላል።—ፊልጵ. 4:6, 7
-
-
ለአምላክ የልቧን አውጥታ ነገረችውበእምነታቸው ምሰሏቸው
-
-
18 ፍናና እንደ ቀድሞው ሐናን ማበሳጨት እንደማትችል የተገነዘበችው መቼ ይሆን? ዘገባው ስለዚህ ጉዳይ የሚገልጸው ነገር ባይኖርም ስለ ሐና ሲናገር “ከዚያም በኋላ በፊቷ ላይ ሐዘን አልታየም” ማለቱ ከዚያ ጊዜ ጀምሮ ይበልጥ ደስተኛ እንደሆነች ያመለክታል። ያም ሆነ ይህ ፍናና፣ የክፋት ድርጊቷ ምንም ውጤት እንዳላስገኘ ወዲያው ተገነዘበች። መጽሐፍ ቅዱስ ከዚያ በኋላ ስሟን አይጠቅስም።
-