-
ኤልያስ እውነተኛውን አምላክ አስከበረመጠበቂያ ግንብ—1998 | ጥር 1
-
-
የበኣል ነቢያት “በሠሩት መሠዊያ ዙሪያ እያነከሱ ያሸበሽቡ” ጀመር። ከጠዋትም እስከ ቀትር ድረስ “በኣል ሆይ፣ ስማን” እያሉ የበኣልን ስም ጠሩ። በኣል ግን ምንም መልስ አልሰጠም። (1 ነገሥት 18:26) በዚህን ጊዜ ኤልያስ “አምላክ ነውና በታላቅ ቃል ጩኹ” በማለት ያላግጥባቸው ጀመር። (1 ነገሥት 18:27) የበኣል አምላኪዎች ሰውነታቸውን በቢላዋና በጩቤ እንኳ ሳይቀር ይተለትሉ ጀመር። ይህ ልማድ የአማልክቶቻቸውን ርኅራሄ ለማነሳሳት አብዛኛውን ጊዜ አረማውያን የሚጠቀሙበት ዘዴ ነው።b—1 ነገሥት 18:28
-
-
ኤልያስ እውነተኛውን አምላክ አስከበረመጠበቂያ ግንብ—1998 | ጥር 1
-
-
b አንዳንዶች የራስን ሰውነት ሆን ብሎ መጉዳት ሰውን መሥዋዕት አድርጎ ከማቅረብ ልማድ ጋር ዝምድና እንዳለው ይገልጻሉ። እነዚህን ተግባሮች የሚፈጽሙት አካላዊ ሥቃይ ወይም ደምን ማፍሰስ የአንድን አምላክ ሞገስ ለማስገኘት ያስችላሉ ተብሎ ይታሰብ ስለነበር ነው።
-