-
ከፍተኛ ወሮታ ያስገኘ ጉብኝትመጠበቂያ ግንብ—1999 | ሐምሌ 1
-
-
የሳባ ንግሥት በሰሎሞን ጥበብና በመንግሥቱ ብልጽግና ከመደነቋ የተነሳ “ነፍስ አልቀረላትም” ነበር። (1 ነገሥት 10:4, 5) አንዳንዶች ይህን ሐረግ ንግሥቲቱ “እስትንፋሷ ቀጥ አለ” ማለት እንደሆነ አድርገው ይረዱታል። እንዲያውም አንድ ሃይማኖታዊ ምሁር ሕሊናዋን እንደሳተች ተናግረዋል! ያም ሆነ ይህ ንግሥቲቱ ባየችውና በሰማችው ነገር ተደንቃ ነበር። የሰሎሞን አገልጋዮች የዚህን ንጉሥ ጥበብ መስማት በመቻላቸው ደስተኞች መሆናቸውን ከመግለጿም በላይ ሰሎሞንን በማንገሡ ይሖዋን ባርካለች። ከዚያም ለንጉሡ በጣም ውድ ስጦታዎች የሰጠችው ሲሆን ወርቁ ብቻ እንኳ አሁን ባለው የዋጋ ተመን 40,000,000 የአሜሪካ ዶላር ያወጣል። ሰሎሞንም ስጦታዎች በማምጣት “የወደደችውን ሁሉ ከእርሱም የለመነችውን ሁሉ” ለንግሥቲቱ ሰጣት።c—1 ነገሥት 10:6-13
-
-
ከፍተኛ ወሮታ ያስገኘ ጉብኝትመጠበቂያ ግንብ—1999 | ሐምሌ 1
-
-
c አንዳንዶች ይህ አባባል ንግሥቲቱ ከሰሎሞን ጋር የጾታ ግንኙነት ፈጽማለች ማለት እንደሆነ ያስባሉ። አልፎ ተርፎም ወንድ ልጅ እንደወለዱ በአፈ ታሪክ ይነገራል። ይሁን እንጂ እነዚህን ሐሳቦች የሚደግፍ ምንም ማስረጃ የለም።
-