የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • እስከ መጨረሻው ጸንቷል
    በእምነታቸው ምሰሏቸው
    • አካዝያስ የበቀል እርምጃ ለመውሰድ ቆርጦ ስለተነሳ ኤልያስን እንዲያስሩት አንድ ሃምሳ አለቃና በሥሩ ያሉትን 50 ሰዎች ላከ። ሰዎቹ ኤልያስን “ተራራው አናት ላይ ተቀምጦ” አገኙት፤a ሃምሳ አለቃውም “ንጉሡ ‘ና ውረድ’ ብሎሃል” የሚል ቀጭን ትእዛዝ ለኤልያስ አስተላለፈ። ይህን ሲል ኤልያስ ከተራራው ወርዶ ወደሚገደልበት ቦታ አብሯቸው እንዲሄድ ማዘዙ ሊሆን ይችላል። እስቲ አስበው! እነዚያ ወታደሮች ኤልያስ “የእውነተኛው አምላክ ሰው” እንደሆነ ቢያውቁም ሊያስፈራሩት ሞከሩ። እነዚህ ሰዎች ምንኛ ተሳስተዋል! ኤልያስ፣ ሃምሳ አለቃውን “እኔ የአምላክ ሰው ከሆንኩ እሳት ከሰማይ ወርዶ አንተንና ከአንተ ጋር ያሉትን 50 ሰዎች ይብላ” አለው። ይሖዋም እርምጃ ወሰደ! “እሳት ከሰማይ ወርዶ [ሃምሳ አለቃውንና] 50ዎቹን ሰዎች በላ።” (2 ነገሥት 1:9, 10) የእነዚህ ወታደሮች አሟሟት፣ ይሖዋ የእሱን አገልጋዮች የሚያቃልሉ ወይም የሚንቁ ሰዎችን በቸልታ እንደማያልፍ የሚያሳይ ግልጽ ማስጠንቀቂያ ነው።—1 ዜና መዋዕል 16:21, 22

  • እስከ መጨረሻው ጸንቷል
    በእምነታቸው ምሰሏቸው
    • ኤልያስ በዙሪያው ያሉ ሰዎች ግትርና ዓመፀኛ ቢሆኑም እሱ በጽናት ይሖዋን ማገልገሉን እንዲቀጥል የረዳው ምንድን ነው? የዚህን ጥያቄ መልስ ማወቃችን ለእኛም ጠቃሚ ነው። አንድ የምትወደው ሰው የሰጠኸውን መልካም ምክር አልሰማ ብሎ መጥፎ የሆነ አካሄድ መከተሉን በመቀጠሉ ስሜትህ ተጎድቶ ያውቃል? እንዲህ ያለውን አሳዛኝ ሁኔታ መቋቋም የሚቻለው እንዴት ነው? ወታደሮቹ ኤልያስን ያገኙት “ተራራው አናት ላይ” መሆኑ የሚሰጠን ትምህርት ይኖር ይሆን? ኤልያስ ወደ ተራራው የወጣው ለምን እንደሆነ በእርግጠኝነት መናገር አንችልም፤ ሆኖም እንደ እሱ ላለ የጸሎት ሰው እንዲህ ያለው ጸጥታ የሰፈነበት ቦታ ወደ አምላኩ ይበልጥ ለመቅረብ የሚያስችል ጥሩ አጋጣሚ እንደሚፈጥርለት ጥርጥር የለውም። (ያዕቆብ 5:16-18) እኛም በተመሳሳይ ብቻችንን ሆነን አምላክን የምናነጋግርበት ቋሚ ጊዜ መመደብ ይኖርብናል፤ በዚህ ጊዜ አምላክን በስሙ እየጠራን ችግራችንን እና ጭንቀታችንን ሁሉ አውጥተን ልናካፍለው እንችላለን። እንዲህ ማድረጋችን በዙሪያችን ያሉት ሰዎች ሞኝነት የተንጸባረቀበትና ጎጂ የሆነ አካሄድ ቢከተሉም እንኳ እኛ በጽናት እንድንቀጥል ይረዳናል።

  • እስከ መጨረሻው ጸንቷል
    በእምነታቸው ምሰሏቸው
    • a አንዳንድ ምሁራን፣ እዚህ ላይ የተጠቀሰው ተራራ የቀርሜሎስ ተራራ እንደሆነ ይናገራሉ፤ ኤልያስ ከአምላክ ባገኘው ኃይል ከተወሰኑ ዓመታት በፊት የባአልን ነቢያት በዚህ ተራራ ላይ ድል አድርጎ ነበር። እርግጥ መጽሐፍ ቅዱስ፣ ኤልያስ በዚህ ወቅት የትኛው ተራራ ላይ እንደነበረ አይናገርም።

አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
ውጣ
ግባ
  • አማርኛ
  • አጋራ
  • የግል ምርጫዎች
  • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
  • የአጠቃቀም ውል
  • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
  • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
  • JW.ORG
  • ግባ
አጋራ