የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • ኤልያስ ግፍ በበዛበት ዘመን ጸንቶ ኖሯል
    መጠበቂያ ግንብ—2014 | የካቲት 1
    • ኤልዛቤል ስለጠነሰሰችው ሴራ ስናነብ ‘ምን ያህል ክፉ ናት’ ብለን መደነቃችን አይቀርም። ንግሥት ኤልዛቤል፣ ከባድ ክስ የቀረበበት አንድ ሰው በአምላክ ሕግ መሠረት ጥፋተኛ ለመባል የግድ ሁለት ሰዎች ሊመሠክሩበት እንደሚገባ ታውቃለች። (ዘዳግም 19:15) ስለዚህ በናቡቴ ላይ በሐሰት ለመመሥከር ፈቃደኛ የሆኑ ሁለት ሰዎች እንዲፈልጉ የሚያዝ በአክዓብ ስም የተጻፈ ደብዳቤ በኢይዝራኤል ላሉ ትልቅ ቦታ ያላቸው ሰዎች ላከች፤ ምሥክሮቹ ‘አምላክን ሲሳደብ ሰምተነዋል’ ብለው የሚመሠክሩ ሲሆን ይህ ደግሞ በሞት የሚያስቀጣ ጥፋት ነበር። የሚያሳዝነው እቅዷ ሰመረላት። ሁለት “ምናምንቴ ሰዎች” (የ1954 ትርጉም) በናቡቴ ላይ በሐሰት መሠከሩበትና በድንጋይ ተወግሮ ተገደለ። ይህም እንዳይበቃ ደግሞ የናቡቴ ወንዶች ልጆችም ተገደሉ!b (1 ነገሥት 21:5-14፤ ዘሌዋውያን 24:16፤ 2 ነገሥት 9:26) አክዓብ የራስነት ሥልጣኑን ሚስቱ እንዳሻት እንድትጠቀምበት አሳልፎ የሰጣት ሲሆን እሷም እነዚያን ንጹሕ ሰዎች አጥፍታለች።

  • ኤልያስ ግፍ በበዛበት ዘመን ጸንቶ ኖሯል
    መጠበቂያ ግንብ—2014 | የካቲት 1
    • b ኤልዛቤል የናቡቴን ልጆች ለማስገደል እንድትነሳሳ ያደረጋት የወይን እርሻውን እነሱ እንዳይወርሱ የነበራት ፍራቻ ሊሆን ይችላል። አምላክ እንዲህ ያሉ የጭቆና ድርጊቶችን የፈቀደበትን ምክንያት ለማወቅ በዚህ እትም ውስጥ የሚገኘውን “አንባቢያን የሚያነሱት ጥያቄ” የሚለውን ርዕስ ተመልከት።

አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
ውጣ
ግባ
  • አማርኛ
  • አጋራ
  • የግል ምርጫዎች
  • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
  • የአጠቃቀም ውል
  • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
  • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
  • JW.ORG
  • ግባ
አጋራ