የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • የሌሎችን መንፈስ የምታድስ ነህ?
    መጠበቂያ ግንብ—2007 | ኅዳር 15
    • የሌሎችን መንፈስ የምታድስ ነህ?

      ሊባኖስንና ሶርያን በሚያዋስነው አንቲ-ሊባነን በሚባለው የተራራ ሰንሰለት ደቡባዊ ጫፍ ላይ ከባሕር ወለል በላይ 2,814 ሜትር የሚደርስ አስደናቂ ከፍታ ያለው የአርሞንዔም ተራራ ይገኛል። የተራራው ጫፍ በዓመት ውስጥ ለበርካታ ወራት በበረዶ የሚሸፈን ሲሆን ይህም በምሽት የሚነፍሰው እርጥበት ያዘለ ሞቃት አየር በአናቱ ላይ ሲያልፍ እንዲቀዘቅዝና ጤዛ እንዲፈጥር ምክንያት ይሆናል። ጤዛው ከተራራው በታች ወዳሉት ፈር ወደተባሉት የዛፍ ዓይነቶችና ሌሎች የፍራፍሬ ዛፎች ቁልቁል ይወርዳል። ከዚያም ከዛፎቹ በታች ወደሚገኙት የወይን ተክሎች ይሰርጋል። ለረጅም ወራት በሚዘልቀው የጥንቷ እስራኤል የበጋ ወቅት ለዕፅዋቱ ዋነኛ የውኃ ምንጭ ሆኖ የሚያገለግለው ሕይወትን የሚያድሰው ይህ ጠል ነበር።

      በአምላክ መንፈስ አነሳሽነት በተዘመረ አንድ መዝሙር ላይ በይሖዋ አምላኪዎች መካከል የሚታየው መንፈስን የሚያድስ አንድነት ‘በጽዮን ተራራ ላይ በሚወርደው የአርሞንዔም ጠል’ ተመስሏል። (መዝሙር 133:1, 3) የአርሞንዔም ተራራ ለዕጽዋት ሕይወትን የሚያድስ ጠል እንደሚሰጥ ሁሉ እኛም የምናገኛቸውን ሰዎች መንፈስ ልናድስ እንችላለን። እንዲህ ማድረግ የምንችለው እንዴት ነው?

  • የሌሎችን መንፈስ የምታድስ ነህ?
    መጠበቂያ ግንብ—2007 | ኅዳር 15
    • [በገጽ 16 ላይ የሚገኝ ሥዕል]

      ከአርሞንዔም ተራራ ላይ የሚወርደው ጠል የዕፅዋትን ሕይወት ያድሳል

አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
ውጣ
ግባ
  • አማርኛ
  • አጋራ
  • የግል ምርጫዎች
  • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
  • የአጠቃቀም ውል
  • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
  • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
  • JW.ORG
  • ግባ
አጋራ