-
የይሖዋ ቤተሰብ ውድ የሆነ አንድነት አለውመጠበቂያ ግንብ—1996 | ሐምሌ 15
-
-
4. መዝሙር 133 ስለ ወንድማማች አንድነት የሚናገረውን በራስህ አባባል እንዴት ትገልጸዋለህ?
4 መዝሙራዊው ዳዊት የወንድማማች አንድነትን በጣም ከፍ አድርጎ ተመልክቶታል። እንዲያውም በመንፈስ አነሣሽነት ተገፋፍቶ ስለዚህ ጉዳይ ዘምሯል! በገናውን ይዞ እንዲህ ብሎ ሲዘምር በዓይነ ሕሊናህ ተመልከተው፦ “ተመልከቱ! ወንድሞች ስምም ሆነው በኅብረት ሲቀመጡ ምንኛ መልካምና ምንኛ ያማረ ነው! (አዓት) ከራስ እስከ ጢም እንደሚፈስስ፣ እስከ አሮን ጢም፣ በልብሱ መደረቢያም እንደሚወርድ ሽቱ ነው። በጽዮን ተራሮች እንደሚወርድ እንደ አርሞንዔም ጠል ነው፤ በዚያ እግዚአብሔር በረከቱን ሕይወትንም እስከ ዘላለም አዝዞአልና።”—መዝሙር 133:1-3
-
-
የይሖዋ ቤተሰብ ውድ የሆነ አንድነት አለውመጠበቂያ ግንብ—1996 | ሐምሌ 15
-
-
6, 7. የእስራኤላውያን አንድነት እንደ አርሞንዔም ተራራ ጠል የነበረው እንዴት ነው? ዛሬ የአምላክ በረከት የት ሊገኝ ይችላል?
6 እስራኤላውያን ስምም ሆነው አንድ ላይ መሰንበታቸው እንደ አርሞንዔም ጠል ሊሆን የቻለው እንዴት ነው? ይህ ተራራ ከባሕር ወለል በላይ 2,800 ሜትር ከፍታ ያለው በመሆኑ ዓመቱን ሙሉ ማለት ይቻላል፣ በበረዶ የተሸፈነ ነው። በአርሞንዔም ተራራ ጫፍ ላይ ያለው በረዶ የሌሊቱን ተን እንዲቀዘቅዝና ከፍተኛ ጤዛ እንዲፈጠር በማድረግ ለረጅም ጊዜ በሚቆየው የበጋ ወቅት ተክሎች እንዳይደርቁ ይረዳል። ከአርሞንዔም ሸንተረር ላይ የሚነሳው እርጥበት አዘል አየር የሚተነውን ውኃ በደቡብ በኩል እስከ ኢየሩሳሌም ድረስ ሊወስደው ይችላል፤ በዚህ ሥፍራ ውኃው ወደ ጠልነት ይለወጣል። ስለዚህ መዝሙራዊው ‘በጽዮን ተራሮች ላይ ስለሚወርደው የአርሞንዔም ጠል’ የተናገረው ነገር ትክክል ነው። የይሖዋ አምላኪዎችን ቤተሰባዊ አንድነት የሚያጠናክረውን የሚያነቃቃ መንፈስ የሚያስታውስ እንዴት ያለ ግሩም መግለጫ ነው!
7 የክርስቲያን ጉባኤ ከመቋቋሙ በፊት ጽዮን ወይም ኢየሩሳሌም የእውነተኛ አምልኮ ማዕከል ነበረች። በመሆኑም አምላክ በረከቱ እንዲፈስ ያዘዘው በዚያ ነበር። የበረከቶች ሁሉ ምንጭ የሆነው አምላክ ይገኝ የነበረው እሱን ይወክለው በነበረውና ኢየሩሳሌም ውስጥ በነበረው ቤተ መቅደስ በመሆኑ በረከቶቹም ከዚያ መፍሰስ ነበረባቸው። በአሁኑ ጊዜ ግን እውነተኛ አምልኮ በአንድ ቦታ የተወሰነ ባለመሆኑ የአምላክ አገልጋዮች ያላቸው በረከት፣ ፍቅርና አንድነት በመላው ምድር ላይ ይገኛል። (ዮሐንስ 13:34, 35) ለዚህ አንድነት አስተዋጽኦ ያደረጉት አንዳንድ ነገሮች ምንድን ናቸው?
-