የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • የይሖዋን በጎች እንዲጠብቁ የተሾሙ ‘ስጦታ የሆኑ ወንዶች’
    መጠበቂያ ግንብ—1999 | ሰኔ 1
    • 10. ሌሎችን ማስተካከል ምንን ይጨምራል?

      10 ይሖዋ የሚያስተካክሉንን ‘ስጦታ የሆኑ ወንዶች’ የሰጠን ሽማግሌዎች በመንፈሳዊ የሚያነቃቁና ለሕዝቡ ምሳሌ ይሆናሉ በሚል ነው። (1 ቆሮንቶስ 16:​17, 18፤ ፊልጵስዩስ 3:​17) ሌሎችን ማስተካከል ማለት የተሳሳተ አካሄድ የሚከተሉትን ማረም ብቻ ሳይሆን ታማኝ የሆኑትም ከትክክለኛው ጎዳና እንዳይወጡ መርዳትንም የሚያካትት ነው።a የምንኖረው ተስፋ የሚያስቆርጡ በርካታ ችግሮች በሞሉበት ጊዜ እንደመሆኑ ብዙዎች ጸንተው እንዲቀጥሉ ማበረታቻ ማግኘት ያስፈልጋቸዋል። አንዳንዶች አስተሳሰባቸው ከአምላክ አስተሳሰብ ጋር እንዲስማማ ጥንቃቄ የተሞላበት እርዳታ ማግኘት ሊያስፈልጋቸው ይችላል። ለምሳሌ ያህል አንዳንድ ታማኝ ክርስቲያኖች ጥልቅ ከሆነ የዋጋቢስነት ወይም የከንቱነት ስሜት ጋር ይታገላሉ። እነዚህ “የተጨነቁ ነፍሳት” ይሖዋ ፈጽሞ እንደማይወዳቸውና ከልብ ተጨንቀው የሚያቀርቡትን አገልግሎት እንኳ እንደማይቀበል ሆኖ ሊሰማቸው ይችላል። (1 ተሰሎንቄ 5:​14 NW) ሆኖም ይህ ዓይነቱ አስተሳሰብ አምላክ ለአገልጋዮቹ ካለው ስሜት ፈጽሞ የራቀ ነው።

  • የይሖዋን በጎች እንዲጠብቁ የተሾሙ ‘ስጦታ የሆኑ ወንዶች’
    መጠበቂያ ግንብ—1999 | ሰኔ 1
    • a “ማስተካከል” ተብሎ የተተረጎመው ይኸው ቃል በግሪኩ የሴፕቱጀንት ትርጉም በመዝሙር 17[16]:​5 ላይ የተሠራበት ሲሆን እዚያ ላይም ታማኙ ዳዊት አረማመዱ ከይሖዋ ጎዳና ሳይወጣ ጸንቶ እንዲቆም ጸልዮአል።

አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
ውጣ
ግባ
  • አማርኛ
  • አጋራ
  • የግል ምርጫዎች
  • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
  • የአጠቃቀም ውል
  • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
  • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
  • JW.ORG
  • ግባ
አጋራ