የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • የአምላክን ፈቃድ እያደረግህ ነውን?
    መጠበቂያ ግንብ—1994 | መጋቢት 1
    • የአምላክን ፈቃድ ከማድረግ የሚገኘውን ደስታ ጠብቆ ማቆየት

      በጥንቷ እስራኤል ይኖር የነበረው ንጉሥ ዳዊት በሕይወቱ ሁሉ የአምላክን ፈቃድ ለማድረግ የጣረ ሰው ነበር። በእርሱ ላይ ብዙ አስቸጋሪ ሁኔታዎችና ተጽዕኖዎች የደረሱበት ቢሆንም “አምላኬ ሆይ፣ ፈቃድህን ለማድረግ ወደድሁ፣ ሕግህም በልቤ ውስጥ ነው” ብሎ እንዲናገር በመንፈስ አነሣሽነት ተገፋፍቶ ነበር። (መዝሙር 40:8) የይሖዋን ፈቃድ የማድረግ ጉዳይ በዳዊት ሁለንተና ማለትም በነፍሱ ሁሉ ውስጥ ነበር። ይሖዋን ከማገልገል ያገኝ የነበረው ደስታ አንድም ጊዜ ያልተቀነሰበት ምሥጢር ይህ ነበር። የአምላክን ፈቃድ ማድረግ ለዳዊት አስቸጋሪ ነገር አልነበረም። ከዚህ ይልቅ፣ ዘወትር የሚያስደስተውና ከልቡ የሚመነጭ ነገር ነበር። ምንም እንኳ አንዳንድ ጊዜ ኃጢአት ቢሠራና ድክመት ቢያሳይም በሕይወቱ ሁሉ አምላኩን ይሖዋን ለማገልገል የሚችለውን ሁሉ ለማድረግ ታግሏል።

      አንዳንድ ጊዜ ደስታችን ሊቀንስብን ይችላል። ልንደክም ወይም ተስፋ ልንቆርጥ እንችላለን። ምናልባትም ከዚህ በፊት ያደረግናቸው ስሕተቶች ድቅን እያሉ ያስቸግሩን ይሆናል። ባለፉት ጊዜያት የፈጸምናቸው የስሕተት ድርጊቶች የሕሊና መረበሽ ያስከትሉብን ይሆናል። ብዙውን ጊዜ እንደዚህ ያሉትን ስሜቶች የአምላክን ቃል ይበልጥ በማጥናት ማሸነፍ ይቻላል። ዳዊት እንዳደረገው የአምላክን ሕግ በእኛ “ውስጥ” ለመቅረጽ መጣር ይኖርብናል። የአምላክን ፈቃድ ባለን ችሎታ ሁሉ በሙሉ ነፍስ ለማድረግ የምንሞክር ከሆነ እርሱ ታማኝ ስለሆነ የሚገባንን ዋጋ ይሰጠናል።—ኤፌሶን 6:6፤ ዕብራውያን 6:10–12፤ 1 ጴጥሮስ 4:19

      ሐዋርያው ጳውሎስ በመዝሙር 40:6–8 ላይ የሚገኙት የዳዊት ቃሎች በኢየሱስ ክርስቶስ ላይ እንደ ተፈጸሙ በዕብራውያን 10:5–7 ላይ መጥቀሱን ማስተዋል ይገባል። በዚህም ኢየሱስ ከአባቱ ጋር ምን ያህል ቅርበት እንደነበረው አመልክቷል። “ፈቃድ” ተብሎ የተተረጎመው የዕብራይስጥ ቃል ‘ደስታ፣ ምኞት፣ ሞገስ ወይም ፍስሐ’ የሚል ሐሳብ ያስተላልፋል። ስለዚህ ስለ ክርስቶስ የሚናገረው መዝሙር 40:8 “አምላኬ ሆይ፣ ደስ የሚያሰኝህን ነገር ለማድረግ ወደድሁ” ተብሎ ሊነበብ ይችላል።a ኢየሱስ አባቱ የሚደሰትበትን ነገር ለማድረግ ፈልጎ ነበር። ኢየሱስ ያደረገው ከእሱ የሚጠበቀውን ብቻ አልነበረም። የአባቱን ልብ ደስ የሚያሰኘውን ሁሉ አድርጓል። ይህን በማድረጉም ተደስቷል።

      የኢየሱስ ሕይወት ሌሎች ሰዎች የአምላክ ፈቃድ ምን እንደሆነ እንዲያውቁና የአምላክን በረከቶች ለማግኘት ምን ማድረግ እንደሚኖርባቸው በማስተማር ላይ ያተኮረ ነበር። የሙሉ ጊዜ ሰባኪና አስተማሪ በመሆንና ይህንንም ሥራ በመሥራት ታላቅ ደስታ አግኝቷል። ስለዚህ የይሖዋን ሥራ በብዛት በሠራን መጠን ብዙ ደስታ እንደምናገኝ የታወቀ ነው። አንተስ፣ ደስታህ እንዲበዛልህ በስብከቱ ሥራ ሙሉ ጊዜ ልታገለግል ትችላለህን?

  • የአምላክን ፈቃድ እያደረግህ ነውን?
    መጠበቂያ ግንብ—1994 | መጋቢት 1
    • a በመዝሙር 40:8 ላይ ያለውን የግርጌ ማስታወሻ ተመልከት።

አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
ውጣ
ግባ
  • አማርኛ
  • አጋራ
  • የግል ምርጫዎች
  • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
  • የአጠቃቀም ውል
  • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
  • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
  • JW.ORG
  • ግባ
አጋራ