-
‘እቅድህ ሁሉ ይሳካልሃል’መጠበቂያ ግንብ—2007 | ግንቦት 15
-
-
መዝሙራዊው ዳዊት ባቀናበረው መዝሙር ላይ እንዲህ ሲል ጸልዮአል:- “አምላኬ ሆይ፤ ንጹሕ ልብ ፍጠርልኝ፤ ቀና የሆነውንም መንፈስ በውስጤ አድስ። የማዳንህን ደስታ መልስልኝ፤ በእሽታ መንፈስም ደግፈህ ያዘኝ።” (መዝሙር 51:10, 12) ከቤርሳቤህ ጋር ከፈጸመው ኃጢአት ንስሐ የገባው ዳዊት እዚህ ጥቅስ ላይ ይሖዋ አምላክ ልቡን እንዲያነጻለትና ትክክል የሆነውን ማድረግ እንዲችል መንፈሱን ማለትም የአእምሮ ዝንባሌውን እንዲያድስለት ለምኗል።
ይሖዋ በእርግጥ ንጹሕ ልብ በመፍጠር ቀናና እሺ ባይ የሆነውን መንፈስ በውስጣችን ሊያድስልን ይችላል? ወይስ እያንዳንዳችን ንጹሕ ልብ ለማግኘትና ይዘን ለመኖር ጥረት ማድረግ ይኖርብናል? እርግጥ ነው፣ ይሖዋ “ልብን ይመረምራል።” ይሁን እንጂ በልባችን ውስጥ ያለውን ሐሳብ ለመለወጥ ጣልቃ የሚገባው ምን ያህል ነው? (ምሳሌ 17:3፤ ኤርምያስ 17:10) ይሖዋ በሕይወታችን፣ በውስጣዊ ግፊታችንና በድርጊታችን ላይ ምን ያህል ተጽዕኖ ያሳድራል?
-
-
‘እቅድህ ሁሉ ይሳካልሃል’መጠበቂያ ግንብ—2007 | ግንቦት 15
-
-
‘ልብን ማዘጋጀት’ ያለበት ማን ነው?
ምሳሌ 16:1ሀ “የልብ ዕቅድ [“ዝግጅት፣” NW] የሰው ነው” በማለት ይናገራል። ከዚህ በግልጽ ማየት እንደሚቻለው ‘ልብን ማዘጋጀት’ የእያንዳንዳችን ኃላፊነት ነው። ይሖዋ በተአምራዊ መንገድ ልባችንን አያዘጋጅልንም ወይም የእሺ ባይነት መንፈስ አይሰጠንም። ከቃሉ ከመጽሐፍ ቅዱስ ላይ ትክክለኛ እውቀት ለማግኘት፣ በተማርነው ላይ ለማሰላሰልና አስተሳሰባችንን ከእርሱ አስተሳሰብ ጋር ለማስማማት ጥረት ማድረግ ያስፈልገናል።—ምሳሌ 2:10, 11
ዳዊት “ንጹሕ ልብ” እና ‘ቀና መንፈስ’ እንዲሰጠው መጠየቁ የኃጢአት ዝንባሌ እንዳለውና ልቡን ከዚህ ለማንጻት መለኮታዊ እርዳታ እንደሚያስፈልገው መገንዘቡን የሚያሳይ ነው። ፍጽምና የጎደለን ሰዎች በመሆናችን ‘የሥጋ ሥራዎችን’ እንድንፈጽም ልንፈተን እንችላለን። (ገላትያ 5:19-21) እንደ ‘ዝሙት፣ ርኩሰት፣ ፍትወት፣ ክፉ ምኞትና መጐምጀት የመሳሰሉትን ምድራዊ ምኞቶቻችንን ለመግደል’ የይሖዋ እርዳታ ያስፈልገናል። (ቈላስይስ 3:5) ወደ መጥፎ ድርጊቶች ከሚመሩ ፈተናዎች ለመጠበቅና የኃጢአት ዝንባሌዎችን ከልባችን ለማስወገድ እንዲረዳን ወደ ይሖዋ መጸለያችን ምንኛ አስፈላጊ ነው!
-