-
ከይሖዋ ጋር ተቀራርባችሁ ኑሩመጠበቂያ ግንብ—1991 | ታኅሣሥ 15
-
-
1. ጸሎትን በሚመለከት የይሖዋ ፈቃድ ምንድን ነው? ሐዋርያው ጳውሎስስ ስለ መጸለይ ምን ማበረታቻ ሰጥቷል?
ይሖዋ ለታማኝ ሕዝቡ በሙሉ “ተስፋ የሚሰጥ አምላክ” ነው። “ጸሎት ሰሚ” በመሆኑ በፊታቸው ያስቀመጠላቸውን አስደሳች ተስፋ እንዲጨብጡ እንዲረዳቸው የሚያቀርቡትን ልመና ይሰማቸዋል። (ሮሜ 15:13፤ መዝሙር 65:2) አገልጋዮቹን ሁሉ በፈለጉበት በማናቸውም ሰዓት ወደሱ እንዲቀርቡ በቃሉ በመጽሐፍ ቅዱስ በኩል ያበረታታቸዋል። ከልብ የሚያሳስባቸውን ጉዳይ ለመስማት ምንጊዜም ዝግጁ ነው። እንዲያውም “በጸሎት እንዲጸኑና” “ያለማቋረጥ እንዲጸልዩ” ያበረታታቸዋል።a (ሮሜ 12:12፤ 1 ተሰሎንቄ 5:17) ይሖዋ ሁሉም ክርስቲያኖች ዘወትር በጸሎት እንዲያነጋግሩት፣ በተወዳጅ ልጁ በኢየሱስ ክርስቶስ ስም ልባቸውን ለሱ እንዲያፈሱ ፈቃዱ ነው።—ዮሐንስ 14:6, 13, 14
-
-
ከይሖዋ ጋር ተቀራርባችሁ ኑሩመጠበቂያ ግንብ—1991 | ታኅሣሥ 15
-
-
3 ደቀ መዝሙሩ ያዕቆብ “ወደ እግዚአብሔር ቅረቡ ወደ እናንተም ይቀርባል” በማለት ጽፏል። (ያዕቆብ 4:8) አምላክ ልዑል ቢሆንምና እኛም ፍጽምና የጐደለን ብንሆንም ለሱ የምንናገረውን ለመስማት እስከማይችል ድረስ በንቀት አይመለከተንም ወይም ራሱን ከእኛ አያርቅም። (ሥራ 17:27) በተጨማሪም ግዴለሽ ወይም ደንታቢስ አይደለም። መዝሙራዊው “የይሖዋ ዓይኖች ወደ ጻድቃን ናቸውና ጆሮቹም ለጸሎታቸው ተከፍተዋል” ይላል።—መዝሙር 34:15፤ 1 ጴጥሮስ 3:12
4. የይሖዋን ጸሎት አድማጭነት እንዴት በምሳሌ ማስረዳት ይችላል?
4 ይሖዋ እንድንጸልይ ይጋብዘናል። ፀሎትን በርካታ ሰዎች አንድ ላይ ሆነው በሚያወሩበት ጊዜ ከሚኖረው ሁኔታ ጋር ልናወዳድር እንችላለን። አንተም ሌሎች ሲያወሩ ለመስማት እዚያ ቦታ ነህ እንበል። ያንተ ሥራ ግን መመልከት ወይም መታዘብ ብቻ ነው እንበል። ነገር ግን በዚህ ጊዜ አንዱ ወዳንተ ዞር ብሎ ስምህን ጠርቶ ቢያነጋግርህ ትኩረትህን በተለየ መንገድ ይስበዋል። በተመሳሳይም አምላክ ሕዝቡ በየትኛውም ስፍራ ያሉ ቢሆኑ ትኩረቱ ሁልጊዜ ወደነሱ ነው። (2 ዜና 16:9፤ ምሳሌ 15:3) ስለዚህ ሁልጊዜ እየተከላከለልንና እየጠበቀን ቃሎቻችንን በትኩረት ያዳምጣል። ይሁን እንጂ በጸሎት የአምላክን ስም በምንጠራበት ጊዜ ትኩረቱ ሙሉ በሙሉ ይሳብና እኛን ብቻ ልዩ በሆነ ሁኔታ ያዳምጣል። ይሖዋ ታላቅ ኃይል ስላለው ድምፅ ሳያሰማ በልቡና በአእምሮው ብቻ የሚጸልየውን ሰው ልመናዎች እንኳ ሳይቀር ማየትና መረዳት ይችላል። አምላክ በቅንነት ስሙን ወደሚጠሩና ከሱ ጋር ተቀራርበው ለመኖር ወደሚፈልጉ ሰዎች ሁሉ እንደሚቀርብ አረጋግጦልናል።—መዝሙር 145:18
-