-
ይሖዋ ዕድሜያችንን እንዴት እንደምንቆጥር ያስተምረናልመጠበቂያ ግንብ—2001 | ኅዳር 15
-
-
9. መዝሙራዊው የሰው ልጆችን የአንድ ሺህ ዓመት ዕድሜ ከምን ጋር አወዳድሮታል?
9 በመንፈስ አነሳሽነት የጻፈው መዝሙራዊ የሰው ልጆችን የአንድ ሺህ ዓመት ዕድሜ ዘላለማዊ በሆነው ፈጣሪ ፊት በጣም አጭር ከሆነ የጊዜ ርዝማኔ ጋር አወዳድሮታል። አምላክን በማስመልከት እንዲህ በማለት ጽፏል:- “ሰዎችን ወደ ዐፈር [“ትቢያ፣” NW ] ትመልሳለህ፤ ‘የሰው ልጆች ሆይ፤ ወደ ቦታችሁ ተመለሱ’ ትላለህ፤ ሺህ ዓመት በፊትህ፣ እንዳለፈችው እንደ ትናንት ቀን፣ እንደ ሌሊትም እርቦ ነውና።”—መዝሙር 90:3, 4 አ.መ.ት
-
-
ይሖዋ ዕድሜያችንን እንዴት እንደምንቆጥር ያስተምረናልመጠበቂያ ግንብ—2001 | ኅዳር 15
-
-
11. ለእኛ ረዥም መስሎ የሚታየን ጊዜ በአምላክ ዘንድ በጣም አጭር የሆነው ለምንድን ነው?
11 ከይሖዋ አንጻር ሲታይ 969 ዓመት የኖረው ማቱሳላ እንኳ የኖረው ከአንድ ቀን ያነሰ ጊዜ ነው። (ዘፍጥረት 5:27) በአምላክ ዘንድ አንድ ሺህ ዓመት ሲያልፍ የ24 ሰዓት ርዝማኔ ያለው አንድ ቀን ያለፈ ያህል ነው። በተጨማሪም መዝሙራዊው አንድ ሺህ ዓመት በአምላክ ፊት አንድ ጠባቂ በጥበቃ ሥራ ከሚቆይበት ከአንድ ሌሊት እርቦ ጋር እኩል እንደሆነ ተናግሯል። (መሳፍንት 7:19) ከዚህ ለመረዳት እንደሚቻለው ለእኛ ረዥም መስሎ የሚታየን ጊዜ ዘላለማዊ በሆነው አምላክ በይሖዋ ዘንድ በጣም አጭር መሆኑን ነው።
-