የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • ‘ባረጁ ጊዜ ያፈራሉ’
    መጠበቂያ ግንብ—2007 | መስከረም 15
    • ‘ባረጁ ጊዜ ያፈራሉ’

      በሜድትራንያን አካባቢ የሚኖሩ አብዛኞቹ ሰዎች ግቢያቸው ውስጥ የተምር ዛፎችን ይተክላሉ። እነዚህ ዛፎች በውበታቸውና በሚያፈሩት ጣፋጭ ፍሬ ይታወቃሉ። ከዚህም በላይ ከመቶ ለሚበልጡ ዓመታት ያለማቋረጥ ፍሬ ይሰጣሉ።

  • ‘ባረጁ ጊዜ ያፈራሉ’
    መጠበቂያ ግንብ—2007 | መስከረም 15
    • በዘንባባ ዛፍ የተመሰሉት ውብ የሆኑ ሴቶች ብቻ አይደሉም። መዝሙራዊው እንዲህ ሲል ዘምሯል:- “ጻድቃን እንደ ዘንባባ ይንሰራፋሉ፤ እንደ ሊባኖስ ዝግባም ይንዠረገጋሉ። በእግዚአብሔር ቤት ተተክለዋል፤ በአምላካችንም አደባባይ ይንሰራፋሉ። ባረጁ ጊዜ እንኳ ያፈራሉ፤ እንደ ለመለሙና እንደ ጠነከሩም ይኖራሉ።”—መዝሙር 92:12-14

      አምላክን በታማኝነት የሚያገለግሉ አረጋውያን ውብ ከሆነው የዘንባባ ዛፍ ጋር የሚያመሳስሏቸው ብዙ ነገሮች አሏቸው። መጽሐፍ ቅዱስ “ሽበት የክብር ዘውድ ነው፤ የሚገኘውም በጽድቅ ሕይወት ነው” ይላል። (ምሳሌ 16:31) አረጋውያን በዕድሜ መግፋት ሳቢያ ጉልበታቸው ቢደክምም፣ የአምላክ ቃል የሆነውን መጽሐፍ ቅዱስን አዘውትረው በማጥናት መንፈሳዊ ጥንካሬያቸውን እንደያዙ መቀጠል ይችላሉ። (መዝሙር 1:1-3፤ ኤርምያስ 17:7, 8) ታማኝ አረጋውያን የሚናገሯቸው ማራኪ ቃላትና መልካም ምሳሌነታቸው ለሌሎች ከፍተኛ የብርታት ምንጭ ከመሆን ባሻገር ከዓመት እስከ ዓመት ፍሬ ማፍራታቸውን ይቀጥላሉ። (ቲቶ 2:2-5፤ ዕብራውያን 13:15, 16) አረጋውያንም ልክ እንደ ዘንባባ ዛፍ በስተ እርጅናቸው ፍሬ ማፍራት ይችላሉ።

አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
ውጣ
ግባ
  • አማርኛ
  • አጋራ
  • የግል ምርጫዎች
  • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
  • የአጠቃቀም ውል
  • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
  • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
  • JW.ORG
  • ግባ
አጋራ