-
ጥበብን አግኝ ተግሣጽንም ተቀበልመጠበቂያ ግንብ—1999 | መስከረም 15
-
-
የምሳሌ መጽሐፍ ዋነኛ ዓላማ በመክፈቻ ቃላቱ ውስጥ ተብራርቷል። “የእስራኤል ንጉሥ የዳዊት ልጅ የሰሎሞን ምሳሌዎች፤ ጥበብንና ተግሣጽን ለማወቅ፣ የእውቀትንም ቃል ለማስተዋል፣ የጥበብን ትምህርት ጽድቅንና ፍርድን ቅንነትንም ለመቀበል፣ ብልሃትን ለአላዋቂዎች ይሰጥ ዘንድ ለጐበዛዝትም እውቀትንና ጥንቃቄን።”—ምሳሌ 1:1-4
-
-
ጥበብን አግኝ ተግሣጽንም ተቀበልመጠበቂያ ግንብ—1999 | መስከረም 15
-
-
ጥበብ እውቀትን፣ ማስተዋልን፣ ብልህነትንና የማሰብ ችሎታን ጨምሮ የብዙ ነገሮች ጥምረት ነው። ማስተዋል አንድን ነገር በጥልቀት የመመልከትና የነገሩን ምንነት ለማወቅ የተለያዩ ክፍሎቹ እርስ በርስ ያላቸውን ግንኙነትና አጠቃላዩን ይዘት በማወቅ መዋቅሩን የመረዳት ችሎታ ነው። ማስተዋል በምክንያት ላይ የተመሠረተ እውቀት ሲሆን አንድ አካሄድ ትክክል ወይም ስህተት የሆነበትን ምክንያት የመረዳት ችሎታ ነው። ለምሳሌ ያህል አንድ አስተዋይ የሆነ ሰው አንድ ሰው ወደ ተሳሳተ አቅጣጫ እያመራ እንዳለ ሊያውቅና በዚያ አቅጣጫ መጓዝ ስለሚያስከትለው አደጋ ቶሎ ብሎ ሊያስጠነቅቀው ይችላል። ይሁን እንጂ ግለሰቡ በዚያ አቅጣጫ ለምን እያመራ እንዳለና ግለሰቡን ለመታደግ የሚያስችል ውጤታማ የሆነ መፍትሔ ማቅረብ እንዲችል የሚረዳው ማስተዋል ነው።
-