-
“ትእዛዜን ጠብቅ በሕይወትም ትኖራለህ”መጠበቂያ ግንብ—2000 | ኅዳር 15
-
-
ቀጥላም “ና፣ እስኪነጋ ድረስ በፍቅር እንርካ፣ በተወደደ መተቃቀፍም ደስ ይበለን” ትለዋለች። ግብዣው ሁለቱ አብረው እራት ከመብላት ያለፈ ነገር እንዲያደርጉ ነው። የጾታ ግንኙነት እንዲፈጽሙ እያግባባችው ነው። ይህ ግብዣ ለዚህ ወጣት እንደ ጀብዱ የሚቆጠር አስደሳች ገጠመኝ ነው! አክላም “ባለቤቴ በቤቱ የለምና፣ ወደ ሩቅ መንገድ ሄዶአልና፤ በእጁም የብር ከረጢት ወስዶአል፤ ሙሉ ጨረቃ በሆነች ጊዜ ወደ ቤቱ ይመለሳል” በማለት ታግባባዋለች። (ምሳሌ 7:18-20) ባለቤትዋ ለሥራ ጉዳይ ወደ ሩቅ አገር ስለሄደና በቅርቡም ስለማይመለስ ምንም የሚያሰጋቸው ነገር እንደሌለ ትነግረዋለች። አንድን ወጣት በማታለል ረገድ እንዴት የተካነች ነች! “በብዙ ጨዋታዋ እንዲስት ታደርገዋለች፤ በከንፈርዋ ልዝብነት ትጐትተዋለች።” (ምሳሌ 7:21) እንደዚህ ባለው ማባበያ ላለመሸነፍ የዮሴፍን ዓይነት የሞራል ጥንካሬ ያስፈልጋል። (ዘፍጥረት 39:9, 12) ወጣቱ ማሸነፍ ይችል ይሆን?
-
-
“ትእዛዜን ጠብቅ በሕይወትም ትኖራለህ”መጠበቂያ ግንብ—2000 | ኅዳር 15
-
-
ንጉሡ የተመለከታት “ጋለሞታ ሴት” ወጣቱን “በተወደደ መተቃቀፍ ደስ ይበለን” ስትል አባብላዋለች። ብዙ ወጣቶች በተለይ ደግሞ ሴቶች በተመሳሳይ መንገድ ጥቃት አልደረሰባቸውም? እስቲ አስበው:- አንድ ሰው የጾታ ብልግና እንድትፈጽም የሚያባብልህ በእውነት አፍቅሮ ነው ወይስ የራስ ወዳድነት ፍላጎቱን ለማርካት? አንዲትን ሴት ከልብ ያፈቀረ ሰው እንዴት ሕሊናዋን የሚያስጥስ ድርጊት እንድትፈጽም ይገፋፋታል? ሰሎሞን “ልብህ ወደ መንገድዋ አያዘንብል” ሲል አጥብቆ መክሯል።
-