-
“ትእዛዜን ጠብቅ በሕይወትም ትኖራለህ”መጠበቂያ ግንብ—2000 | ኅዳር 15
-
-
ሰሎሞን “እርሱ እንዲህ ስቶ ይከተላታል፣ በሬ ለመታረድ እንዲነዳ፣ ውሻም ወደ እስራት እንዲሄድ፣ ወፍ ወደ ወጥመድ እንደሚቸኩል፣ ለነፍሱ ጥፋት እንደሚሆን ሳያውቅ፣ ፍላጻ ጉበቱን እስኪሰነጥቀው ድረስ” በማለት ይናገራል።—ምሳሌ 7:22, 23
ወጣቱ የቀረበለትን ግብዣ እምቢ ማለት አልቻለም። ማስተዋሉ ጠፍቶ ‘ለእርድ እንደሚነዳ በሬ’ ተከትሏት ሄደ። በእግረ ሙቅ የታሰረ ሰው ማምለጥ እንደማይችል ሁሉ ወጣቱም እንዲሁ በማይወጣበት ኃጢአት ውስጥ ሊዘፈቅ ነው። “ፍላጻ ጉበቱን እስኪሰነጥቀው” ማለትም ለሞት ሊዳርገው የሚችል ጉዳት እስኪያገኘው ድረስ አደጋው አይታየውም። በጾታ ግንኙነት ለሚተላለፍ ለሞት የሚዳርግ በሽታ ራሱን ስለሚያጋልጥ ሞቱ ቃል በቃል አካላዊ ሞት ሊሆን ይችላል።a ያጋጠመው ነገር “ለነፍሱ ጥፋት” ስለሚሆንበት ለመንፈሳዊ ሞትም ሊዳርገው ይችላል። መላ እሱነቱንና ሕይወቱን ክፉኛ የሚጎዳ ነገር ከማድረጉም በላይ በአምላክ ላይ ከባድ ኃጢአት ሠርቷል። ወደ ወጥመድ እንደሚቸኩል ወፍ እሱም በሞት መዳፍ ለመያዝ ይጣደፋል!
-
-
“ትእዛዜን ጠብቅ በሕይወትም ትኖራለህ”መጠበቂያ ግንብ—2000 | ኅዳር 15
-
-
a በጾታ ግንኙነት የሚተላለፉ አንዳንድ በሽታዎች ጉበትን ያጠቃሉ። ለምሳሌ ያህል ቂጥኝ ከፍተኛ ደረጃ ላይ ሲደርስ የባክቴሪያው ዘአካላት ጉበት ላይ ከፍተኛ ጉዳት ያስከትላሉ። እንዲሁም ጨብጥ አማጭ ዘአካላት ጉበት እንዲያብጥ ያደርጋሉ።
-