የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • “ይሖዋ ጥበብን ይሰጣል”
    መጠበቂያ ግንብ—1999 | ኅዳር 15
    • በጥንቷ እስራኤል ይኖር የነበረው ጠቢቡ ንጉሥ ሰሎሞን የሚከተለውን በፍቅር ላይ የተመሠረተ አባታዊ ቃላት ሰንዝሯል:- “ልጄ ሆይ፣ ቃሌን ብትቀበል፣ ትእዛዜንም በአንተ ዘንድ ሸሽገህ ብትይዛት፣ ጆሮህ ጥበብን እንዲያደምጥ ታደርጋለህ፣ ልብህንም ወደ ማስተዋል ታዘነብላለህ። ረቂቅ እውቀትን ብትጠራት፣ ለማስተዋልም ድምፅህን ብታነሣ፣ እርስዋንም እንደ ብር ብትፈላልጋት፣ እርስዋንም እንደ ተቀበረ ገንዘብ ብትሻት፤ የዚያን ጊዜ እግዚአብሔርን መፍራት ታውቃለህ፣ የአምላክንም እውቀት ታገኛለህ።”​—⁠ምሳሌ 2:​1-5

  • “ይሖዋ ጥበብን ይሰጣል”
    መጠበቂያ ግንብ—1999 | ኅዳር 15
    • ጥበብ ከአምላክ ያገኘነውን እውቀት ተገቢ በሆነ መንገድ የመጠቀም ችሎታ ነው። መጽሐፍ ቅዱስ ጥበብን ግሩም በሆነ መንገድ ይገልጽልናል። አዎን፣ የጥበብ ቃላት ምሳሌን እና መክብብን በመሰሉ መጻሕፍት ውስጥ ሰፍረው ይገኛሉ። እኛም እነዚህን ቃላት በትኩረት መከታተል ይኖርብናል። በተጨማሪም በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ የአምላክን መሠረታዊ ሥርዓቶች በሥራ ላይ ማዋል ያለውን ዋጋማነት ጎላ አድርገው የሚያሳዩ በርካታ ምሳሌዎችን እናገኛለን። (ሮሜ 15:​4፤ 1 ቆሮንቶስ 10:​11) ለምሳሌ ያህል የነቢዩ ኤልሳዕ አገልጋይ ስለነበረው ስለ ስግብግቡ ግያዝ የሚናገረውን ታሪክ ተመልከት። (2 ነገሥት 5:​20-27) ይህ ታሪክ ስግብግብ ከመሆን መራቅ ጥበብ መሆኑን አያስተምረንም? መጀመሪያ ላይ ምንም ዓይነት ጉዳት የሚያመጣ የማይመስለውን የያዕቆብ ሴት ልጅ ዲና የከነዓን “አገር ሴቶች ልጆች”ን ለማየት መሄዷ ያስከተለው አሳዛኝ ውጤትስ? (ዘፍጥረት 34:​1-31) መጥፎ ጓደኝነት የሚያስከትለውን ጉዳት ከወዲሁ እንድንገነዘብ አያደርገንም?​—⁠ምሳሌ 13:​20፤ 1 ቆሮንቶስ 15:​33

      ጥበብን በትኩረት ለመከታተል ማስተዋልና እውቀት መቅሰም ይኖርብናል። ዌብስተርስ ሪቫይዝድ አንብሪጅድ ዲክሽነሪ እንደሚለው ማስተዋል “አንድን ነገር ከሌላው ለመለየት የሚያስችል የአእምሮ ኃይል ወይም ችሎታ ነው።” አምላካዊ ማስተዋል ትክክል የሆነውን ነገርና ስህተት የሆነውን ነገር ለይቶ የማወቅና ከዚያም ትክክለኛውን ጎዳና የመምረጥ ችሎታ ነው። ‘ልባችንን ወደ ማስተዋል’ ካላዘነበልን ወይም ማስተዋልን ለመቅሰም ጉጉቱ ከሌለን ‘ወደ ሕይወት በሚወስደው መንገድ’ ላይ መጓዛችንን እንዴት ልንቀጥል እንችላለን? (ማቴዎስ 7:​14፤ ከዘዳግም 30:​19, 20 ጋር አወዳድር።) የአምላክን ቃል ማጥናትና በሥራ ላይ ማዋል ማስተዋልን ያስገኛል።

አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
ውጣ
ግባ
  • አማርኛ
  • አጋራ
  • የግል ምርጫዎች
  • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
  • የአጠቃቀም ውል
  • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
  • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
  • JW.ORG
  • ግባ
አጋራ