-
ከአምላካዊ ፍርሃት ጥቅም ማግኘታችሁን ቀጥሉመጠበቂያ ግንብ (የጥናት እትም)—2023 | ሰኔ
-
-
6. ከዚህ በመቀጠል ስለ የትኞቹ ሁለት ምሳሌያዊ ሴቶች እንመለከታለን?
6 ከዚህ በመቀጠል ምሳሌ ምዕራፍ 9ን እንመረምራለን። በዚህ ምዕራፍ ላይ ጥበብና ሞኝነት በሁለት ሴቶች ተመስለዋል። (ከሮም 5:14፤ ገላትያ 4:24 ጋር አወዳድር።) ይህን ምዕራፍ ስንመረምር፣ የሰይጣን ዓለም የሥነ ምግባር ብልግናና ፖርኖግራፊ እንደተጠናወተው በአእምሯችን እንያዝ። (ኤፌ. 4:19) በመሆኑም በቀጣይነት አምላካዊ ፍርሃትን ማዳበራችንና ከክፋት መራቃችን አስፈላጊ ነው። (ምሳሌ 16:6) ወንዶችም ሆንን ሴቶች በዚህ ምዕራፍ ውስጥ ከሚገኘው ምክር ጥቅም ማግኘት እንችላለን። ሁለቱም ሴቶች ተሞክሮ ለሌላቸው ወይም “ማስተዋል ለጎደላቸው” ሰዎች ግብዣ እንደሚያቀርቡ ተደርጎ ተገልጿል። ሁለቱም በምሳሌያዊ ሁኔታ ‘ወደ ቤቴ መጥታችሁ ምግብ ብሉ’ የሚል ግብዣ ያቀርባሉ። (ምሳሌ 9:1, 5, 6, 13, 16, 17) ሆኖም ግብዣውን የሚቀበሉ ሰዎች የሚገጥማቸው ውጤት በእጅጉ የተለያየ ነው።
-
-
ከአምላካዊ ፍርሃት ጥቅም ማግኘታችሁን ቀጥሉመጠበቂያ ግንብ (የጥናት እትም)—2023 | ሰኔ
-
-
“ማስተዋል የጎደላት ሴት” የምታቀርበው ግብዣ አስከፊ መዘዝ ያስከትላል (አንቀጽ 7ን ተመልከት)
7. በምሳሌ 9:13-18 መሠረት አንደኛዋ ሴት የምታቀርበው ግብዣ ወደ ምን ይመራል? (ሥዕሉንም ተመልከት።)
7 በመጀመሪያ “ማስተዋል የጎደላት ሴት” የምታቀርበውን ግብዣ እንመልከት። (ምሳሌ 9:13-18ን አንብብ።) ይህች ኀፍረተ ቢስ ሴት ተሞክሮ የሌላቸውን ሰዎች ወደ እሷ መጥተው ምግብ እንዲበሉ ትጋብዛለች። ውጤቱስ ምንድን ነው? ጥቅሱ “በሞት የተረቱት በዚያ እንዳሉ” ይገልጻል። ምሳሌ መጽሐፍ ውስጥ በሌላ ምዕራፍ ላይ ተመሳሳይ ዘይቤያዊ አገላለጽ እናገኛለን። ያ ምዕራፍ “ጋጠወጥ” እና “ባለጌ” ስለሆነች ሴት ማስጠንቀቂያ ይሰጣል። “ቤቷ ሰውን ይዞ ወደ ሞት ይወርዳል” ይላል። (ምሳሌ 2:11-19) ምሳሌ 5:3-10 ደግሞ ስለ ሌላ “ጋጠወጥ ሴት” ይናገራል፤ እሷም ብትሆን “እግሮቿ ወደ ሞት ይወርዳሉ።”
8. ምን ዓይነት ውሳኔ ሊደቀንብን ይችላል?
8 “ማስተዋል የጎደላት ሴት” የምታቀርበውን ግብዣ የሚሰሙ ሰዎች ግብዣዋን ለመቀበል ወይም ላለመቀበል መወሰን ይኖርባቸዋል። እኛም እንዲህ ያለ ምርጫ ሊደቀንብን ይችላል። የፆታ ብልግና ለመፈጸም ስንፈተን አሊያም ደግሞ ሚዲያ ወይም ኢንተርኔት ላይ የፖርኖግራፊ ምስሎች ድንገት ሲመጡብን ምን ዓይነት ምርጫ እናደርጋለን?
-