የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • ከአምላካዊ ፍርሃት ጥቅም ማግኘታችሁን ቀጥሉ
    መጠበቂያ ግንብ (የጥናት እትም)—2023 | ሰኔ
    • በጥንት ዘመን አንዲት ዝሙት አዳሪ ደጃፏ ጋ ቆማ አንድን ሰውዬ ወደ ቤቷ እንዲገባ ስትጋብዘው።

      “ማስተዋል የጎደላት ሴት” የምታቀርበው ግብዣ አስከፊ መዘዝ ያስከትላል (አንቀጽ 7⁠ን ተመልከት)

      7. በምሳሌ 9:13-18 መሠረት አንደኛዋ ሴት የምታቀርበው ግብዣ ወደ ምን ይመራል? (ሥዕሉንም ተመልከት።)

      7 በመጀመሪያ “ማስተዋል የጎደላት ሴት” የምታቀርበውን ግብዣ እንመልከት። (ምሳሌ 9:13-18⁠ን አንብብ።) ይህች ኀፍረተ ቢስ ሴት ተሞክሮ የሌላቸውን ሰዎች ወደ እሷ መጥተው ምግብ እንዲበሉ ትጋብዛለች። ውጤቱስ ምንድን ነው? ጥቅሱ “በሞት የተረቱት በዚያ እንዳሉ” ይገልጻል። ምሳሌ መጽሐፍ ውስጥ በሌላ ምዕራፍ ላይ ተመሳሳይ ዘይቤያዊ አገላለጽ እናገኛለን። ያ ምዕራፍ “ጋጠወጥ” እና “ባለጌ” ስለሆነች ሴት ማስጠንቀቂያ ይሰጣል። “ቤቷ ሰውን ይዞ ወደ ሞት ይወርዳል” ይላል። (ምሳሌ 2:11-19) ምሳሌ 5:3-10 ደግሞ ስለ ሌላ “ጋጠወጥ ሴት” ይናገራል፤ እሷም ብትሆን “እግሮቿ ወደ ሞት ይወርዳሉ።”

  • ከአምላካዊ ፍርሃት ጥቅም ማግኘታችሁን ቀጥሉ
    መጠበቂያ ግንብ (የጥናት እትም)—2023 | ሰኔ
    • 10 የፆታ ብልግና ለኀፍረት፣ ለከንቱነት ስሜት፣ ላልተፈለገ እርግዝና እንዲሁም ለቤተሰብ መፍረስ ሊዳርግ ይችላል። በእርግጥም፣ ማስተዋል ከጎደላት ሴት ‘ቤትም’ ሆነ ከምታቀርበው ምግብ መራቅ የጥበብ እርምጃ ነው። የፆታ ብልግና የሚፈጽሙ ብዙ ሰዎች ለመንፈሳዊ ሞት ከመዳረጋቸውም በተጨማሪ ቃል በቃል ያለዕድሜያቸው እንዲቀጩ በሚያደርግ በሽታ ሊያዙ ይችላሉ። (ምሳሌ 7:23, 26) ምዕራፍ 9 ቁጥር 18 ላይ ‘እንግዶቿ በመቃብር ጥልቅ ውስጥ እንደሚገኙ’ ይናገራል። ታዲያ ብዙዎች ለዚህ ሁሉ መከራ የሚዳርገውን የዚህችን ሴት አታላይ ግብዣ የሚቀበሉት ለምንድን ነው?—ምሳሌ 9:13-18

  • ከአምላካዊ ፍርሃት ጥቅም ማግኘታችሁን ቀጥሉ
    መጠበቂያ ግንብ (የጥናት እትም)—2023 | ሰኔ
    • በጥንቷ እስራኤል ውስጥ አንዲት ሴት አንድን ባልና ሚስት ቤቷ አስገብታ ጤናማና ማራኪ ምግብ እንዲበሉ ስትጋብዛቸው።

      “እውነተኛ ጥበብ” የምታቀርበውን ግብዣ መቀበል ሕይወት ያስገኛል (ከአንቀጽ 17-18⁠ን ተመልከት)

      17-18. “እውነተኛ ጥበብ” የምታቀርበውን ግብዣ የሚቀበሉ ሰዎች በአሁኑ ጊዜ የትኞቹን በረከቶች እያገኙ ነው? ወደፊትስ ምን ይጠብቃቸዋል? (ሥዕሉንም ተመልከት።)

      17 ይሖዋ ስለ ሁለት ሴቶች የሚናገር ዘይቤያዊ አገላለጽ በመጠቀም አስደሳች የወደፊት ሕይወት ማግኘት የምንችልበትን መንገድ አሳይቶናል። “ማስተዋል የጎደላት” ጯኺ ሴት የምታቀርበውን ግብዣ የሚቀበሉ ሰዎች በድብቅ ብልግና በመፈጸም ደስታ ለማግኘት ይፈልጋሉ። እነዚህን ሰዎች የሚያሳስባቸው የሚያገኙት ቅጽበታዊ ደስታ እንጂ የወደፊት ሕይወታቸው አይደለም። መጨረሻቸው ወደ “መቃብር ጥልቅ” መውረድ ነው።—ምሳሌ 9:13, 17, 18

አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
ውጣ
ግባ
  • አማርኛ
  • አጋራ
  • የግል ምርጫዎች
  • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
  • የአጠቃቀም ውል
  • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
  • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
  • JW.ORG
  • ግባ
አጋራ