-
‘ጻድቅ በረከት ያገኛል’መጠበቂያ ግንብ—2001 | ሐምሌ 15
-
-
በተጨማሪም ጻድቅ ሰው ክፉዎች የሌላቸው የተረጋጋ ሕይወት ይኖረዋል። “ያለ ነውር የሚሄድ ተማምኖ ይሄዳል፤ መንገዱን የሚያጣምም ግን ይታወቃል። በዓይኑ የሚጠቅስ መከራን ያመጣል፤ ደፍሮ የሚገሥጽ ግን ሰላምን ያደርጋል።”—ምሳሌ 10:9, 10
-
-
‘ጻድቅ በረከት ያገኛል’መጠበቂያ ግንብ—2001 | ሐምሌ 15
-
-
ይህም በራስ ወዳድነት ጥቅም ለማግኘት ሲል እምነት የማጉደል ድርጊት የተለየ ነው። አታላይ ሰው ውሸቱን በጠማማ አነጋገር ወይም በሰውነት እንቅስቃሴው ለመሸፈን ጥረት ያደርግ ይሆናል። (ምሳሌ 6:12-14) ተንኮል ባዘለ ሁኔታ ወይም ለማታለል ሲል በዓይኑ ሲጠቅስ የጥቃት ሰለባው ላይ የአእምሮ ጭንቀት ይፈጥርበታል። ሆኖም ፈጥኖም ይሁን ዘግይቶ የዚህ ሰው ጠማማነት ይጋለጣል። ሐዋርያው ጳውሎስ “የአንዳንዶች ሰዎች ኃጢአት የተገለጠ ነው ፍርድንም ያመለክታል፣ ሌሎችን ግን ይከተላቸዋል፤ እንዲሁ መልካም ሥራ ደግሞ የተገለጠ ነው፣ ያልተገለጠም ከሆነ ሊሰወር አይችልም” በማለት ጽፏል። (1 ጢሞቴዎስ 5:24, 25) ይህን ያደረገው ወላጅም ይሁን ወዳጅ ወይም የትዳር ጓደኛ አሊያም የምናውቀው ሌላ ሰው እምነት ማጉደሉ አንድ ቀን ይፋ መውጣቱ አይቀርም። እምነት በማጉደል መጥፎ ስም ያተረፈን ሰው ማን ያምነዋል?
-