-
“ይሖዋ ጥበብን ይሰጣል”መጠበቂያ ግንብ—1999 | ኅዳር 15
-
-
በጥንቷ እስራኤል ይኖር የነበረው ጠቢቡ ንጉሥ ሰሎሞን የሚከተለውን በፍቅር ላይ የተመሠረተ አባታዊ ቃላት ሰንዝሯል:- “ልጄ ሆይ፣ ቃሌን ብትቀበል፣ ትእዛዜንም በአንተ ዘንድ ሸሽገህ ብትይዛት፣ ጆሮህ ጥበብን እንዲያደምጥ ታደርጋለህ፣ ልብህንም ወደ ማስተዋል ታዘነብላለህ። ረቂቅ እውቀትን ብትጠራት፣ ለማስተዋልም ድምፅህን ብታነሣ፣ እርስዋንም እንደ ብር ብትፈላልጋት፣ እርስዋንም እንደ ተቀበረ ገንዘብ ብትሻት፤ የዚያን ጊዜ እግዚአብሔርን መፍራት ታውቃለህ፣ የአምላክንም እውቀት ታገኛለህ።”—ምሳሌ 2:1-5
-
-
“ይሖዋ ጥበብን ይሰጣል”መጠበቂያ ግንብ—1999 | ኅዳር 15
-
-
ጥበብን በትኩረት ለመከታተል ማስተዋልና እውቀት መቅሰም ይኖርብናል። ዌብስተርስ ሪቫይዝድ አንብሪጅድ ዲክሽነሪ እንደሚለው ማስተዋል “አንድን ነገር ከሌላው ለመለየት የሚያስችል የአእምሮ ኃይል ወይም ችሎታ ነው።” አምላካዊ ማስተዋል ትክክል የሆነውን ነገርና ስህተት የሆነውን ነገር ለይቶ የማወቅና ከዚያም ትክክለኛውን ጎዳና የመምረጥ ችሎታ ነው። ‘ልባችንን ወደ ማስተዋል’ ካላዘነበልን ወይም ማስተዋልን ለመቅሰም ጉጉቱ ከሌለን ‘ወደ ሕይወት በሚወስደው መንገድ’ ላይ መጓዛችንን እንዴት ልንቀጥል እንችላለን? (ማቴዎስ 7:14፤ ከዘዳግም 30:19, 20 ጋር አወዳድር።) የአምላክን ቃል ማጥናትና በሥራ ላይ ማዋል ማስተዋልን ያስገኛል።
አንድ ትምህርት በውስጡ የያዛቸው ዘርፎች እርስ በርሳቸውና ከዋናው ትምህርት ጋር ያላቸውን ተዛማጅነት ለማየት የሚያስችል ‘እውቀት መጥራት’ የምንችለው እንዴት ነው? እርግጥ ነው፣ በዕድሜና በተሞክሮ ከፍተኛ እውቀት ማግኘት የሚቻል ቢሆንም ሁልጊዜ ግን በዚህ መንገድ ማግኘት ይቻላል ማለት አይደለም። (ኢዮብ 12:12፤ 32:6-12) “ትእዛዝህን ፈልጌአለሁና ከሽማግሌዎች ይልቅ አስተዋልሁ” በማለት መዝሙራዊው ተናግሯል። ጨምሮም “የቃልህ ፍቺ ያበራል፣ ሕፃናትንም [“ተሞክሮ የሚጎድላቸውንም፣” NW] አስተዋዮች ያደርጋል” በማለት ተናግሯል። (መዝሙር 119:100, 130) ይሖዋ ‘በዘመናት የሸመገለ’ ከመሆኑም በላይ ከሁሉም የሰው ዘር የሚበልጥ እውቀት አለው። (ዳንኤል 7:13) አምላክ ተሞክሮ ለሚጎድለው ሰው እውቀትን በመስጠት በዕድሜ ከሚበልጡት ሰዎች የተሻለ እንዲሆን ሊያደርገው ይችላል። ስለዚህ የአምላክን ቃል መጽሐፍ ቅዱስን ለማጥናትና በሥራ ላይ ለማዋል ትጉዎች መሆን ይኖርብናል።
የምሳሌ መጽሐፍ ሁለተኛ ምዕራፍ “ብትቀበል፣” “ብትይዛት፣” “ብትጠራት፣” “ብትፈላልጋት፣” “ብትሻት” በሚሉ አገላለጾች ምንባቡን ይጀምራል። ጸሐፊው እነዚህን አባባሎች በመድገም ጠበቅ አድርጎ ሊገልጽ የፈለገው ነገር ምንድን ነው? አንድ የማመሳከሪያ መጽሐፍ እንዲህ ይላል:- “እዚህ ላይ ብልሁ ሰው ጥበብን በጥብቅ የመፈለግን አስፈላጊነት ጎላ አድርጎ ገልጿል።” አዎን፣ ጥበብንና የእርሱ ተዛማጅ ባሕርይ የሆኑትን ማስተዋልንና እውቀትን በትጋት መከታተል ይገባናል።
-