-
ጥበብን አግኝ ተግሣጽንም ተቀበልመጠበቂያ ግንብ—1999 | መስከረም 15
-
-
የምሳሌ መጽሐፍ ዋነኛ ዓላማ በመክፈቻ ቃላቱ ውስጥ ተብራርቷል። “የእስራኤል ንጉሥ የዳዊት ልጅ የሰሎሞን ምሳሌዎች፤ ጥበብንና ተግሣጽን ለማወቅ፣ የእውቀትንም ቃል ለማስተዋል፣ የጥበብን ትምህርት ጽድቅንና ፍርድን ቅንነትንም ለመቀበል፣ ብልሃትን ለአላዋቂዎች ይሰጥ ዘንድ ለጐበዛዝትም እውቀትንና ጥንቃቄን።”—ምሳሌ 1:1-4
-
-
ጥበብን አግኝ ተግሣጽንም ተቀበልመጠበቂያ ግንብ—1999 | መስከረም 15
-
-
ብልህ የሆኑ ሰዎች አርቀው ስለሚመለከቱ በቀላሉ አይታለሉም። (ምሳሌ 14:15) አንድን መጥፎ ነገር ቀደም ብለው ሊገነዘቡና ዝግጁ ሆነው ሊጠብቁ ይችላሉ። እንዲሁም ጥበብ ሕይወታችንን በዓላማ መምራት እንችል ዘንድ ጤናማ የሆኑ አስተሳሰቦችንና ሐሳቦችን እንድናፈልቅ ያስችለናል። በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ የሰፈሩት ምሳሌዎች ጥበብንና ተግሣጽን ማወቅ እንችል ዘንድ የተመዘገቡልን በመሆናቸው በእርግጥም ጠቃሚያችን ናቸው። ሌላው ቀርቶ “ተሞክሮ የጎደለው” ሰው ትኩረት ሰጥቶ የመጽሐፍ ቅዱስ ምሳሌዎችን ከተከታተለ ብልህ እንዲሆን፣ ወጣት ከሆነ ደግሞ እውቀትንና የማስተዋል ችሎታን እንዲያገኝ ይረዳዋል።
-