-
የተናደደ ሰው ሲያጋጥመኝ ምን ማድረግ ይኖርብኛል?ንቁ!—2001 | ታኅሣሥ 8
-
-
“በጣም ተናድዶ ነበር። ትንሽ መሆኔን ስላየ ነው መሰለኝ ሊደበድበኝ ፈለገ። ወደ ኋላዬ እየሸሸሁ ‘ቆይ እንጂ! ረጋ በል! ለምንድን ነው የምትመታኝ? ምን አደረግሁህ? ለምን እንደ ተናደድህ እንኳን አላውቅም። ብንነጋገር አይሻልም?’ አልኩት።”—የ16 ዓመቱ ዳዊት
-
-
የተናደደ ሰው ሲያጋጥመኝ ምን ማድረግ ይኖርብኛል?ንቁ!—2001 | ታኅሣሥ 8
-
-
መጽሐፍ ቅዱስ እንዲህ ሲል ጥበብ የተሞላበት ምክር ይሰጣል:- “የለዘበች መልስ ቁጣን ትመልሳለች፤ ሸካራ ቃል ግን ቁጣን ታስነሣለች።” (ምሳሌ 15:1) አዎን፣ ለቁጣ “ሸካራ ቃል” መመለስ ትርፉ ሁኔታውን ማባባስ ነው። የለዘበ መልስ ግን ብዙውን ጊዜ ነገሩ ቀዝቀዝ እንዲል ከማድረጉም በላይ ውጥረቱን ለማርገብ ያስችላል።
በመግቢያው ላይ የተጠቀሰውን ዳዊትን አስታውስ። ጉልበተኛውን ልጅ አግባብቶ የተናደደበትን ምክንያት እንዲነግረው አደረገ። ለካስ ልጁ ምሳው ስለተሰረቀበት መጀመሪያ ባገኘው ሰው ላይ ንዴቱን መወጣቱ ነበር። ዳዊት “እኔን ስለደበደብከኝ ምሳህ አይመለስልህም” ሲል አስረዳው። ከዚያም አብረው ወደ መመገቢያ አዳራሹ እንዲሄዱ ሐሳብ አቀረበ። እንዲህ ሲል ያስታውሳል:- “አስተናጋጅዋን አውቃት ስለነበር ምሳውን ተካሁለት። ተጨባብጠን ተለያየን፣ ከዚያ ጊዜ ወዲህ ለኔ ያለው አመለካከት ተቀይሯል።” የለዘቡ ቃላት ምን ያህል ኃይል እንዳላቸው አስተዋልክ? በምሳሌ መጽሐፍ ላይ እንደተገለጸው “ለስላሳ አንደበት ዐጥንትን ይሰብራል።”—ምሳሌ 25:15 አ.መ.ት
-