-
‘ጥበብ ጥላ ከለላ ነው’መጠበቂያ ግንብ—2007 | ሐምሌ 15
-
-
ጥበብን ማግኘት በአነጋገራችን ላይ ተጽዕኖ የሚያሳድረው እንዴት ነው? ጠቢቡ ንጉሥ እንዲህ በማለት ይነግረናል:- “አንድን ነገር ጠለቅ ብሎ የሚያስተውል መልካም ነገርን ያገኛል፤ በይሖዋ የሚታመንም ደስተኛ ነው። ልቡ ጥበበኛ የሆነ አስተዋይ ይባላል፤ ከንፈሩ ጣፋጭ የሆነም የማሳመን ችሎታ አለው። ጥልቅ ማስተዋል ለባለቤቱ የሕይወት ምንጭ ነው፤ የሞኞች ቅጣት ራሱ ሞኝነታቸው ነው። የጥበበኛ ሰው ልብ፣ አንደበቱ ጥልቅ ማስተዋል እንዲያንጸባርቅ ያደርጋል፤ ለከንፈሩም የማሳመን ቸሎታ ይጨምርለታል።”—ምሳሌ 16:20-23 NW
-
-
‘ጥበብ ጥላ ከለላ ነው’መጠበቂያ ግንብ—2007 | ሐምሌ 15
-
-
“ልቡ ጥበበኛ የሆነ” ሰው “ብልህ” ወይም “አስተዋይ” መባሉ ምንም አያስደንቅም! (ምሳሌ 16:21 አን አሜሪካን ትራንስሌሽን) አዎን፣ ጥልቅ ማስተዋል፣ ለሚያገኙት ሰዎች “የሕይወት ምንጭ” ነው። ይሁንና ስለ ሞኞችስ ምን ለማለት ይቻላል? እነሱ “ጥበብንና ተግሣጽን ይንቃሉ።” (ምሳሌ 1:7) እነዚህ ሰዎች የይሖዋን ተግሣጽ ባለመቀበላቸው ምን ይደርስባቸዋል? ከላይ እንደተመለከትነው ሰሎሞን “የሞኞች ቅጣት ራሱ ሞኝነታቸው ነው” ብሏል። (ምሳሌ 16:22 NW) ሞኞች ተጨማሪ ተግሣጽ የሚቀበሉ ሲሆን ይህ ደግሞ ብዙውን ጊዜ ከበድ ያለ ቅጣት ያስከትልባቸዋል። ከዚህም በላይ ሞኞች በራሳቸው ላይ ችግር፣ ሃፍረትና በሽታ ሊያመጡ አልፎ ተርፎም ያለ ዕድሜያቸው በሞት ሊቀጩ ይችላሉ።
-