-
የአንባቢያን ጥያቄዎችመጠበቂያ ግንብ—1991 | ነሐሴ 1
-
-
የምሳሌ መጽሐፍ የምክር ቃሎችን በተናጠል የያዙ ብዙ ቁጥሮች አሉት። ምሳሌ 27:23 ግን አንድ አይነት ምክር የሚሰጡ የብዙ ቁጥሮች አንድ ክፍል ብቻ ነው። እንዲህ ይላል፦ “የበጐችህን መልክ አስተውለህ እወቅ። በከብቶችህም ላይ ልብህን አኑር ባለጠግነት ለዘላለም አይኖርምና፣ ዘውድም ለትውልድ ሁሉ አይጸናምና። ደረቅ ሣር ታጭዶ አዲስ ለምለም ሣር ይታያል። ከተራራውም ቡቃያ ይሰበስባል። በጐች ለልብስህ፣ ፍየሎችም የእርሻ ዋጋ ይሆናሉ። ለሲሳይህ ለቤተሰቦችም ሲሳይ ለገረዶችህም ምግብ የፍየል ወተት ይበቃል።”—ምሳሌ 27:23-27
-
-
የአንባቢያን ጥያቄዎችመጠበቂያ ግንብ—1991 | ነሐሴ 1
-
-
ብዙዎች እንዳረጋገጡት ከፍተኛ ትርፍ በሚያስገኝ የንግድ እንቅስቃሴ አማካኝነት የተገኘ “ባለጠግነት” ወይም ሀብትና ከሱም ጋር የሚመጣው ክብር (“ዘውድ”) በቀላሉ ሊጠፋ ይችላል። ስለዚህ የጥንት እንስሳትን በመከባከብ ይከተሉት እንደነበረው ዓይነት ቀላል አኗኗር የሚመረጥበት ብዙ ምክንያት አለ። ያ ዓይነት ኑሮ ቀላል ሊባል የሚችለው ጭንቀት የሌለበት በመሆኑ አይደለም። አንድ እረኛ የመንጋውን ሁኔታ ነቅቶ የሚከታተልና ከአደጋ የተጠበቁ መሆናቸውን ማረጋገጥ ያስፈልገው ነበር። (መዝሙር 23:4) ትኩረት ሰጥቶ መንጋውን በሚጠብቅበት ጊዜ የታመመ ወይም የተጐዳ በግ ካገኘ ሕመም የሚያስታግስ ዘይት ይቀባው ነበር። (መዝሙር 23:5፤ ሕዝቅኤል 34:4፤ ዘካርያስ 11:16) አብዛኛውን ጊዜም ልቡን በከብቶቹ ላይ የሚያኖር እረኛ ጥረቱ ውጤት ሊያስገኝና መንጋውም ቀስ በቀስ በቁጥር ሲጨምር ሊያይ ይችል ነበር።
-