-
የአንባቢያን ጥያቄዎችመጠበቂያ ግንብ—1991 | ነሐሴ 1
-
-
የምሳሌ መጽሐፍ የምክር ቃሎችን በተናጠል የያዙ ብዙ ቁጥሮች አሉት። ምሳሌ 27:23 ግን አንድ አይነት ምክር የሚሰጡ የብዙ ቁጥሮች አንድ ክፍል ብቻ ነው። እንዲህ ይላል፦ “የበጐችህን መልክ አስተውለህ እወቅ። በከብቶችህም ላይ ልብህን አኑር ባለጠግነት ለዘላለም አይኖርምና፣ ዘውድም ለትውልድ ሁሉ አይጸናምና። ደረቅ ሣር ታጭዶ አዲስ ለምለም ሣር ይታያል። ከተራራውም ቡቃያ ይሰበስባል። በጐች ለልብስህ፣ ፍየሎችም የእርሻ ዋጋ ይሆናሉ። ለሲሳይህ ለቤተሰቦችም ሲሳይ ለገረዶችህም ምግብ የፍየል ወተት ይበቃል።”—ምሳሌ 27:23-27
-
-
የአንባቢያን ጥያቄዎችመጠበቂያ ግንብ—1991 | ነሐሴ 1
-
-
ታታሪና ጠንቃቃ እረኛ ሊመካበት የሚችል የእርዳታ ምንጭ አለው። እርሱም ይሖዋ ነው። እንዴት? በጐቹን ለመመገብ የሚያስችል በቂ ሣር ሊያስገኙ የሚችሉ ወቅቶችንና ዑደቶችን የሚሰጠው አምላክ ነው። (መዝሙር 145:16) ከወቅቶቹ መለዋወጥ ጋር ለምለሙ ሣር ከሜዳው ሲጠፋ ጠንቃቃው እረኛ በጐቹን የሚያሰማራበት ሣር የሞላበት ከፍታ ቦታ ይፈልጋል።
-