-
የአንባቢያን ጥያቄዎችመጠበቂያ ግንብ—1991 | ነሐሴ 1
-
-
የምሳሌ መጽሐፍ የምክር ቃሎችን በተናጠል የያዙ ብዙ ቁጥሮች አሉት። ምሳሌ 27:23 ግን አንድ አይነት ምክር የሚሰጡ የብዙ ቁጥሮች አንድ ክፍል ብቻ ነው። እንዲህ ይላል፦ “የበጐችህን መልክ አስተውለህ እወቅ። በከብቶችህም ላይ ልብህን አኑር ባለጠግነት ለዘላለም አይኖርምና፣ ዘውድም ለትውልድ ሁሉ አይጸናምና። ደረቅ ሣር ታጭዶ አዲስ ለምለም ሣር ይታያል። ከተራራውም ቡቃያ ይሰበስባል። በጐች ለልብስህ፣ ፍየሎችም የእርሻ ዋጋ ይሆናሉ። ለሲሳይህ ለቤተሰቦችም ሲሳይ ለገረዶችህም ምግብ የፍየል ወተት ይበቃል።”—ምሳሌ 27:23-27
-
-
የአንባቢያን ጥያቄዎችመጠበቂያ ግንብ—1991 | ነሐሴ 1
-
-
ምሳሌ 27:26, 27 የእንዲህ ዓይነቱ ሥራ ውጤት የሆነውን ምግብና ልብስ ይጠቅሳል። እርግጥ እዚህ ላይ የተገለጸው የቅንጦት ምግብ ወይም በጣም ጣፋጭ ሆኖ የተዘጋጀ ልዩ ልዩ ዓይነት ምግብ አይደለም። ወይም ደግሞ ሠራተኛው የዘመኑን ፋሽን የተከተለ በጣም ውድ የሆነ ልብስ እለብሳለሁ ብሎ ተስፋ እንዲያደርግ አያደርገውም። ይሁን እንጂ ጥረት ለማድረግ ፈቃደኛ ከሆነ እረኛውና ቤተሰቡ ከመንጋው ወተት (በዚያውም ዓይብ) እና ጠንካራ ልብስ ለመሥራት የሚያስችል ሱፍ ሊያገኙ ይችሉ ነበር።
-