-
በኃይል አጠቃቀም ረገድ “አምላክን የምትመስሉ ሁኑ”ወደ ይሖዋ ቅረብ
-
-
10. (ሀ) አምላክ ለወላጆች ምን ሥልጣን ሰጥቷል? (ለ) “ተግሣጽ” የሚለው ቃል ምን ትርጉም አለው? እንዴትስ መሰጠት ይኖርበታል? (የግርጌ ማስታወሻውንም ተመልከት።)
10 አምላክ ለወላጆችም የሰጠው ሥልጣን አለ። መጽሐፍ ቅዱስ “አባቶች ሆይ፣ ልጆቻችሁን አታስመርሯቸው፤ ከዚህ ይልቅ በይሖዋ ተግሣጽና ምክር አሳድጓቸው” የሚል ምክር ይሰጣል። (ኤፌሶን 6:4) በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ “ተግሣጽ” የሚለው ቃል “ኮትኩቶ ማሳደግን፣ ማሠልጠንንና ማስተማርን” ሊያመለክት ይችላል። ልጆች በጥሩ ሁኔታ ተኮትኩተው እንዲያድጉ ከተፈለገ በግልጽ የተቀመጡ መመሪያዎችና ደንቦች ሊሰጧቸው ይገባል። መጽሐፍ ቅዱስ እንዲህ ያለውን ተግሣጽ ወይም ማሠልጠኛ ከፍቅር ጋር አያይዞ ይገልጸዋል። (ምሳሌ 13:24) ስለሆነም “የተግሣጽ በትር” የልጆችን ስሜትም ሆነ አካል የሚጎዳ መሆን የለበትም።a (ምሳሌ 22:15፤ 29:15) ድርቅ ያለ ሕግ ማውጣት ወይም ፍቅርና ርኅራኄ የሌለው ተግሣጽ መስጠት የወላጅነት ሥልጣንን አላግባብ መጠቀም ከመሆኑም በላይ የልጁን ስሜት ሊጎዳ ይችላል። (ቆላስይስ 3:21) በሌላ በኩል ግን ልጆች በተገቢው መንገድ ሚዛናዊ የሆነ ተግሣጽ የሚሰጣቸው ከሆነ ወላጆቻቸው እንደሚወዷቸው እንዲሁም ጥሩ ልጆች ሆነው እንዲያድጉ የሚፈልጉ መሆኑን እንዲገነዘቡ ያደርጋቸዋል።
-