የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • በኃይል አጠቃቀም ረገድ “አምላክን የምትመስሉ ሁኑ”
    ወደ ይሖዋ ቅረብ
    • 10. (ሀ) አምላክ ለወላጆች ምን ሥልጣን ሰጥቷል? (ለ) “ተግሣጽ” የሚለው ቃል ምን ትርጉም አለው? እንዴትስ መሰጠት ይኖርበታል? (የግርጌ ማስታወሻውንም ተመልከት።)

      10 አምላክ ለወላጆችም የሰጠው ሥልጣን አለ። መጽሐፍ ቅዱስ “አባቶች ሆይ፣ ልጆቻችሁን አታስመርሯቸው፤ ከዚህ ይልቅ በይሖዋ ተግሣጽና ምክር አሳድጓቸው” የሚል ምክር ይሰጣል። (ኤፌሶን 6:4) በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ “ተግሣጽ” የሚለው ቃል “ኮትኩቶ ማሳደግን፣ ማሠልጠንንና ማስተማርን” ሊያመለክት ይችላል። ልጆች በጥሩ ሁኔታ ተኮትኩተው እንዲያድጉ ከተፈለገ በግልጽ የተቀመጡ መመሪያዎችና ደንቦች ሊሰጧቸው ይገባል። መጽሐፍ ቅዱስ እንዲህ ያለውን ተግሣጽ ወይም ማሠልጠኛ ከፍቅር ጋር አያይዞ ይገልጸዋል። (ምሳሌ 13:24) ስለሆነም “የተግሣጽ በትር” የልጆችን ስሜትም ሆነ አካል የሚጎዳ መሆን የለበትም።a (ምሳሌ 22:15፤ 29:15) ድርቅ ያለ ሕግ ማውጣት ወይም ፍቅርና ርኅራኄ የሌለው ተግሣጽ መስጠት የወላጅነት ሥልጣንን አላግባብ መጠቀም ከመሆኑም በላይ የልጁን ስሜት ሊጎዳ ይችላል። (ቆላስይስ 3:21) በሌላ በኩል ግን ልጆች በተገቢው መንገድ ሚዛናዊ የሆነ ተግሣጽ የሚሰጣቸው ከሆነ ወላጆቻቸው እንደሚወዷቸው እንዲሁም ጥሩ ልጆች ሆነው እንዲያድጉ የሚፈልጉ መሆኑን እንዲገነዘቡ ያደርጋቸዋል።

  • በኃይል አጠቃቀም ረገድ “አምላክን የምትመስሉ ሁኑ”
    ወደ ይሖዋ ቅረብ
    • a “በትር” ተብሎ የተተረጎመው የዕብራይስጥ ቃል በመጽሐፍ ቅዱስ ዘመን አንድ እረኛ በጎቹን ለመምራት የሚጠቀምበትን ዱላ ወይም ዘንግ ያመለክታል። (መዝሙር 23:4) በተመሳሳይም ወላጆች የሚጠቀሙበት “በትር” በፍቅር መመሪያ መስጠትን እንጂ በጭካኔ ወይም በኃይል መደብደብን አያመለክትም።

አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
ውጣ
ግባ
  • አማርኛ
  • አጋራ
  • የግል ምርጫዎች
  • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
  • የአጠቃቀም ውል
  • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
  • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
  • JW.ORG
  • ግባ
አጋራ