-
ለገንዘብ ሊኖረን የሚገባው ተገቢ አመለካከት ምንድን ነው?ንቁ!—2007 | ሰኔ
-
-
የመጽሐፍ ቅዱስ አመለካከት
ለገንዘብ ሊኖረን የሚገባው ተገቢ አመለካከት ምንድን ነው?
መጽሐፍ ቅዱስ ‘ገንዘብ ጥላ ከለላ ነው’ ይላል። (መክብብ 7:12) ገንዘብን ለምግብ፣ ለልብስና ለመጠለያ የሚያስፈልጉንን ወጪዎች ለመሸፈን ስለምንጠቀምበት ከድህነት ጋር ተያይዘው ከሚመጡ አስቸጋሪ ሁኔታዎች የሚጠብቀን ጥላ ከለላ ሊሆን ይችላል። በእርግጥም ገንዘብ ከቁሳዊ ነገሮች አንጻር ማንኛውንም ነገር ለመግዛት ያስችላል። መክብብ 10:19 “ገንዘብም ካለ ሁሉ ነገር አለ” ይላል።
-
-
ለገንዘብ ሊኖረን የሚገባው ተገቢ አመለካከት ምንድን ነው?ንቁ!—2007 | ሰኔ
-
-
ከገንዘብ የሚሻል ነገር
ንጉሥ ሰሎሞን ገንዘብ ጥላ ከለላ እንደሆነ ከገለጸ በኋላ “ጥበብም ጥላ ከለላ ነው” በማለት ተናግሯል። እንደዚህ ያለበትን ምክንያት ሲገልጽ “ጥበብ የባለቤቷን ሕይወት መጠበቋ ነው” ብሏል። (መክብብ 7:12) ሰሎሞን እንዲህ ሲል ምን ማለቱ ነበር? ትክክለኛ በሆነ የቅዱሳን ጽሑፎች እውቀትና ጤናማ በሆነ አምላካዊ ፍርሃት ላይ ስለተመሠረተ ጥበብ መናገሩ ነበር። እንዲህ ያለው ጥበብ ከገንዘብ በላቀ መልኩ አንድን ሰው በሕይወቱ ውስጥ ሊያጋጥሙት ከሚችሉ በርካታ መሰናክሎች አልፎ ተርፎም ያለ ዕድሜ በሞት ከመቀጨት ሊጠብቀው ይችላል። እንዲሁም እውነተኛ ጥበብ ልክ እንደ ዘውድ ለባለቤቱ ከፍ ያለ ክብርና ሞገስ ያስገኝለታል። (ምሳሌ 2:10-22፤ 4:5-9) በተጨማሪም ይህ ጥበብ አንድ ሰው የአምላክን ሞገስ እንዲያገኝ ስለሚያስችለው “የሕይወት ዛፍ” ተብሎ ተጠርቷል።—ምሳሌ 3:18
ይህንን ጥበብ ከልባቸው የሚፈልጉ እንዲሁም ለማግኘት ጥረት የሚያደርጉ ሰዎች በቀላሉ ሊገኝ እንደሚችል ይገነዘባሉ። “ልጄ ሆይ . . . የመለየት ጥበብን ብትማጠን፣ ድምፅህን ከፍ አድርገህ ማስተዋልን ብትጣራ፣ እርሷንም እንደ ብር ብትፈልጋት፣ እንደ ተሸሸገ ሀብት አጥብቀህ ብትሻት፣ በዚያን ጊዜ ፈሪሃ እግዚአብሔርን ትረዳለህ፤ አምላክንም ማወቅ ታገኛለህ። እግዚአብሔር ጥበብን ይሰጣልና፤ ከአንደበቱም ዕውቀትና ማስተዋል ይወጣል።”—ምሳሌ 2:1-6
-