የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • “እጅግ ብዙ ሰዎች” ወደ አምላክ ድርጅት የሚወስደውን “ጐዳና” ያዙ
    “የሰላሙ መስፍን“ ሲገዛ በምድር ዙሪያ የሚገኝ ዋስትና ያለው ሕይወት
    • ምሳሌያዊ የዔድን ገነትን ማስገኘት

      4, 5. (ሀ) በዘመናችን ተትቶ የነበረ አንድ ምድር ተመሳሳይ ለውጥ ያደረገው መቼ ነበር? ለምንስ? (ለ) የቅቡዓን ቀሪዎች መልሶ የመገንባት እንቅስቃሴዎች ያስገኙት ምንን ነበር? (ሐ) ኢሳይያስ 35:5–7 የታደሰውን መንፈሳዊ ሁኔታቸውን የገለጸው እንዴት ነው?

      4 በመንፈሳዊ ሁኔታ ምድሪቱ በአምላክ እንደተተወች ከሚያሳየው መልኳ የይሖዋን ሞገስ እንደገና ማግኘቷን ወደሚያረጋግጥ ሁኔታ የመለወጡ ዘመናዊ ተመሳሳይነት በ1919 መፈጸም ጀምሯል። ወደ ቀድሞ ሁኔታቸው የተመለሱት የይሖዋ ሕዝቦች በዚያን ጊዜ በተከፈተው የሰላም ወቅት ሙሉ በሙሉ ለመጠቀም ቆርጠው ነበር። ታላቁ ቂሮስ ኢየሱስ ክርስቶስና አባቱ ይሖዋ አምላክ ነፃ የወጡትን የመንፈሳዊ እስራኤላውያን ቀሪዎች ከ537 ከዘአበ በኋላ ወደ ምድራቸው የተመለሱት የጥንት እስራኤል ቀሪዎች የይሖዋን ቤተ መቅደስ ከመገንባታቸው ጋር ተመሳሳይ የሆነውን አስደናቂ ሥራ ሰጣቸው። ከ1919 በኋላ የተከናወኑ መልሶ የመገንባት እንቅስቃሴዎች ምሳሌያዊ የዔድን ገነትን አስገኝተዋል።

      5 ይህም በሚከተሉት የኢሳይያስ 35 ቃላት ውስጥ ተተንብዮአል:- “በዚያን ጊዜም የዕውሮች ዓይን ይገለጣል የደንቆሮችም ጆሮ ይከፈታል። በዚያን ጊዜ አንካሳ እንደ ሚዳቋ ይዘላል፣ የድዳም ምላስ ይዘምራል፤ በምድረበዳ ውኃ፣ በበረሀም ፈሳሽ ይፈልቃልና። ደረቂቱ ምድር ኩሬ፣ የጥማት መሬት የውኃ ምንጭ ትሆናለች፤ ቀበሮ የተኛበት መኖሪያ ልምላሜና ሸምበቆ ደንገልም ይሆንበታል።”— ኢሳይያስ 35:5–7

  • “እጅግ ብዙ ሰዎች” ወደ አምላክ ድርጅት የሚወስደውን “ጐዳና” ያዙ
    “የሰላሙ መስፍን“ ሲገዛ በምድር ዙሪያ የሚገኝ ዋስትና ያለው ሕይወት
    • 5 ይህም በሚከተሉት የኢሳይያስ 35 ቃላት ውስጥ ተተንብዮአል:- “በዚያን ጊዜም የዕውሮች ዓይን ይገለጣል የደንቆሮችም ጆሮ ይከፈታል። በዚያን ጊዜ አንካሳ እንደ ሚዳቋ ይዘላል፣ የድዳም ምላስ ይዘምራል፤ በምድረበዳ ውኃ፣ በበረሀም ፈሳሽ ይፈልቃልና። ደረቂቱ ምድር ኩሬ፣ የጥማት መሬት የውኃ ምንጭ ትሆናለች፤ ቀበሮ የተኛበት መኖሪያ ልምላሜና ሸምበቆ ደንገልም ይሆንበታል።”— ኢሳይያስ 35:5–7

  • “እጅግ ብዙ ሰዎች” ወደ አምላክ ድርጅት የሚወስደውን “ጐዳና” ያዙ
    “የሰላሙ መስፍን“ ሲገዛ በምድር ዙሪያ የሚገኝ ዋስትና ያለው ሕይወት
    • 8. በሴዳር ፖይንት ኦሀዮ የተደረጉት ሁለት ትልልቅ ስብሰባዎች እንደገና በተደራጁት ቀሪዎች መንፈሳዊ ጆሮዎችና ምላሶች ላይ ምን ውጤት ነበራቸው?

      8 በ1919 እና በ1922 በሴዳር ፖይንት ኦሀዮ ባደረጓቸው ስብሰባዎቻቸው ላይ በፊታቸው ስለተዘረጋው ሥራ ተነገራቸው። በፊታቸው ላለው ሥራ ተዘጋጁ። መንፈሳዊ ጆሮቻቸውም የሚነሽጠውን የአምላክን መንግሥት መልእክት ለመስማትና እርሱን የማወጁን አስፈላጊነት ለመረዳት ተከፍተው ነበር። ለረጅም ጊዜ ሲጸልዩለት ለነበረው መንግሥት እንደ ምስክሮች ሆነው ለማገልገል በተገቢ መንገድ ልክ እንደሚዳቋ ዘልለው ነበር። እስከዚህን ጊዜ ድረስ ዲዳ የነበረው ምላሳቸውም በሰማይ ላይ ሥልጣን ስለያዘው ስለ ሰማያዊው መሲሐዊ መንግሥት በደስታ መጮኽ ጀመረ።— ራእይ 14:1–6

      9. በመንፈሳዊ ሁኔታ ውኃ በምድረበዳ የፈለቀው እንዴት ነበር?

      9 አዎን፣ ሁኔታው አስቀድሞ ደረቅና ጠፍ በነበረ መንፈሳዊ መሬት ላይ ውኃ እንደፈለቀ ያህል ሆኖ ነበር፤ ስለዚህ አሁን ሁሉም ነገር በጣም ስለ ለመለመ ፍሬ ለመስጠት የተዘጋጀ ለምለም ሜዳ መስሎ ነበር። ወደ ቀድሞ ሁኔታቸው የተመለሱት የይሖዋ ሕዝብ በጋለ ሁኔታ ተደስተውና ወደ ከፍታዎች በኃይል እንደሚወጣ ሚዳቋ ጥንካሬ ተሰምቷቸው ነበር! በእርግጥም በ1914 በክርስቶስ መመራት ስለጀመረችው ስለተቋቋመችው የአምላክ መንግሥት የሚገልጹት የእውነት ውኃዎች ከፍተኛ እርካታን በማምጣት እየጨመረ በሚመጣ ኃይል ጐርፈዋል።— ኢሳይያስ 44:1–4

አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
ውጣ
ግባ
  • አማርኛ
  • አጋራ
  • የግል ምርጫዎች
  • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
  • የአጠቃቀም ውል
  • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
  • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
  • JW.ORG
  • ግባ
አጋራ