የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • በደስታ እልል የምንልበት ምክንያት አለን
    መጠበቂያ ግንብ—1996 | የካቲት 15
    • “ሐሤትንና ደስታን ያገኛሉ፣ ኀዘንና ትካዜም ይሸሻሉ።”—ኢሳይያስ 35:10

  • በደስታ እልል የምንልበት ምክንያት አለን
    መጠበቂያ ግንብ—1996 | የካቲት 15
    • 3. ትኩረት ልንሰጣቸው የሚገቡ ትልቅ ትርጉም ያላቸው ቃላት የትኞቹ ናቸው? ለምንስ?

      3 ኢየሱስ “ይህን የነገርሁአችሁ ደስታዬ በእናንተ እንዲሆንና የእናንተም ደስታ ፍጹም እንዲሆን ነው” በማለት የተናገራቸውን ቃላት አስታውስ። (ዮሐንስ 15:11 የ1980 ትርጉም) “የእናንተም ደስታ ፍጹም እንዲሆን” ብሏል። እንዴት ያለ ግሩም አባባል ነው! ስለ ክርስቲያናዊ አኗኗር ያደረግነው ጥልቅ ጥናት ደስታችን ፍጹም ወይም የተሟላ እንዲሆን የሚያደርጉ በርካታ ምክንያቶች አሳይቶን ነበር። አሁን ግን ኢሳይያስ 35:10 ላይ የሚገኙትን ትልቅ ትርጉም ያላቸው ቃላት ልብ በል። እነዚህ ቃላት ትልቅ ትርጉም አላቸው የተባለው በዛሬው ጊዜ በእኛ ላይ እየተፈጸሙ ስለሆነ ነው። እንዲህ ይነበባል፦ “እግዚአብሔርም የተቤዣቸው ይመለሳሉ እየዘመሩም ወደ ጽዮን ይመጣሉ፤ የዘላለም [“ላልተወሰነ ጊዜ” አዓት] ደስታ በራሳቸው ላይ ይሆናል፤ ሐሤትንና ደስታን ያገኛሉ፣ ኀዘንና ትካዜም ይሸሻሉ።”

      4. በኢሳይያስ 35:10 ላይ የተጠቀሰው ምን ዓይነት ደስታ ነው? ለዚህ ደስታ ትኩረት መስጠት ያለብን ለምንድን ነው?

      4 “ላልተወሰነ ጊዜ መደሰት።” “ላልተወሰነ ጊዜ” የሚለው ሐረግ ኢሳይያስ በዕብራይስጥ ቋንቋ ላሰፈረው ቃል ትክክለኛ ትርጉም ነው። ሆኖም ሌሎች ጥቅሶች እንደሚያሳዩት ይህ ጥቅስ የሚያስተላልፈው ጽንሰ ሐሳብ “ለዘላለም” የሚል ነው። (መዝሙር 45:6፤ 90:2፤ ኢሳይያስ 40:28) ስለዚህ ዘላለማዊ ደስታ በሚያስገኙ ሁኔታዎች ሥር ፍጻሜ የሌለው ደስታ ይኖራል። ይህ በጣም ደስ አያሰኝምን? ምናልባት ይህ ጥቅስ ሊጨበጥ ስለማይችል ረቂቅ ሁኔታ የሚናገር መስሎ ይታይህ ይሆናል። ‘ይህ ነገር የሚያጋጥሙኝን የዕለት ተዕለት ችግሮችና አሳሳቢ ጉዳዮች የሚመለከት አይደለም’ በማለት ታስብ ይሆናል። እውነታዎቹ የሚያሳዩት ግን ከዚህ የተለየ ነው። በኢሳይያስ 35:10 ላይ የተሰጠው ትንቢታዊ ተስፋ በዛሬው ጊዜ ለአንተም ትርጉም አለው። ትርጉሙ ምን እንደሆነ ለማወቅ ይህን ማራኪ የሆነ የኢሳይያስ ምዕራፍ 35 ትንቢት በእያንዳንዱ ጥቅስ ላይ በማተኮር እንመርምር። የምንመለከተው ነገር በጣም እንደሚያስደስትህ እርግጠኛ ሁን።

አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
ውጣ
ግባ
  • አማርኛ
  • አጋራ
  • የግል ምርጫዎች
  • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
  • የአጠቃቀም ውል
  • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
  • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
  • JW.ORG
  • ግባ
አጋራ