-
አሁንና ለዘላለም ደስተኛ መሆንመጠበቂያ ግንብ—1996 | የካቲት 15
-
-
17, 18. ገነት በአሁኑ ጊዜ ያለው በምን ዓይነት ሁኔታ ነው? ይህስ የእኛን ሕይወት እንዴት ይነካል?
17 ከቁጥር 1 እስከ 8 የሚገኙት ትንቢቶች በጊዜያችን በመፈጸም ላይ መሆናቸውን ሳንዘነጋ ኢሳይያስ ምዕራፍ 35ን መመርመር እንችላለን። በመንፈሳዊ ገነት ውስጥ እንደምንኖር ግልጽ አይደለምን? ይህ ገነት ገና ፍጹም አልሆነም። ቢሆንም ቁጥር 2 እንደሚናገረው በዚህ ገነት ውስጥ “የእግዚአብሔር ክብር፣ የአምላካችንንም ግርማ” ለማየት ስለቻልን እውነተኛ ገነት ነው። ውጤቱ ምንድን ነው? ቁጥር 10 እንዲህ ይላል፦ “እግዚአብሔርም የተቤዣቸው ይመላለሳሉ እየዘመሩም ወደ ጽዮን ይመጣሉ፤ የዘላለም ደስታ በራሳቸው ላይ ይሆናል፤ ሐሤትንና ደስታን ያገኛሉ፣ ኀዘንና ትካዜም ይሸሻሉ።” ከሐሰት ሃይማኖት ወጥተንና እውነተኛውን አምልኮ ተቀብለን በአምላክ ሞገስ ሥር መኖራችን በእርግጥም በእጅጉ የሚያስደስት ነገር ነው።
-
-
አሁንና ለዘላለም ደስተኛ መሆንመጠበቂያ ግንብ—1996 | የካቲት 15
-
-
24. በኢሳይያስ 35:10 ላይ የተሰጠውን ሐሳብ የምትቀበለው ለምንድን ነው?
24 ኢሳይያስ “እግዚአብሔርም የተቤዣቸው ይመለሳሉ እየዘመሩም ወደ ጽዮን ይመጣሉ፤ የዘላለም ደስታ በራሳቸው ላይ ይሆናል” በማለት ያረጋግጥልናል። ስለዚህ በደስታ እልል የምንልባቸው ምክንያቶች እንዳሉን ሁላችንም እንስማማለን። ይሖዋ በመንፈሳዊ ገነታችን ውስጥ ለሕዝቡ በማድረግ ላይ ባለውና በቅርቡ በሚቋቋመው ምድራዊ ገነት ውስጥ ያደርጋል ብለን ተስፋ በምናደርጋቸው ነገሮች የተነሳ ደስ ይለናል። ኢሳይያስ ደስተኞች የሆንነውን እኛን በተመለከተ “ሐሤትንና ደስታን ያገኛሉ፣ ኀዘንና ትካዜም ይሸሻሉ” በማለት ጽፏል።—ኢሳይያስ 35:10
-