-
“እርቅ እንፍጠር”የኢሳይያስ ትንቢት—ለመላው የሰው ዘር የፈነጠቀ ብርሃን ጥራዝ 1
-
-
1, 2. ይሖዋ የኢየሩሳሌምንና የይሁዳን ሕዝብ ገዥዎች ያወዳደራቸው ከማን ጋር ነው? ይህስ ተገቢ የሆነው ለምንድን ነው?
የኢየሩሳሌም ነዋሪዎች በኢሳይያስ 1:1-9 ላይ ተመዝግቦ የሚገኘውን ውግዘት ከሰሙ በኋላ ለማስተባበል ይዳዳቸው ይሆናል። ለይሖዋ ያቀረቧቸውን መሥዋዕቶች ሁሉ በጉራ ለመዘርዘር እንደሚቃጣቸውም ጥርጥር የለውም። ይሁን እንጂ ከኢሳይያስ 1 ቁጥር 10 እስከ 15 ላይ ይሖዋ እንዲህ ላለው አመለካከታቸው የሚሰጠውን ኩምሽሽ የሚያደርግ መልስ እናገኛለን። እንዲህ በማለት ይጀምራል:- “እናንተ የሰዶም አለቆች ሆይ፣ የእግዚአብሔርን ቃል ስሙ፤ እናንተ የገሞራ ሕዝብ ሆይ፣ የአምላካችንን ሕግ አድምጡ።”—ኢሳይያስ 1:10
2 የሰዶምና ገሞራ ሰዎች የጠፉት ልቅ በሆነው የፆታ ልማዳቸው ምክንያት ብቻ ሳይሆን ልበ ደንዳናና ትዕቢተኛ ስለ ነበሩም ጭምር ነው። (ዘፍጥረት 18:20, 21፤ 19:4, 5, 23-25፤ ሕዝቅኤል 16:49, 50) የኢሳይያስ አድማጮች ከእነዚያ የተረገሙ ከተሞች ሰዎች ጋር መመሳሰላቸው አስደንግጧቸው መሆን አለበት።a የሆነ ሆኖ ይሖዋ የሕዝቡን እውነተኛ ማንነት ያያል። ኢሳይያስም የእነርሱን ‘ጆሮ ለመኮርኮር’ ሲል የአምላክን መልእክት አለዝቦ አይነግራቸውም።—2 ጢሞቴዎስ 4:3 NW
-
-
“እርቅ እንፍጠር”የኢሳይያስ ትንቢት—ለመላው የሰው ዘር የፈነጠቀ ብርሃን ጥራዝ 1
-
-
a የጥንቶቹ አይሁዳውያን ወግ እንደሚለው ከሆነ ክፉ የነበረው ንጉሥ ምናሴ፣ ነቢዩ ኢሳይያስ በመጋዝ ተሰንጥቆ እንዲሞት አድርጓል። (ከዕብራውያን 11:37 ጋር አወዳድር።) አንድ ጽሑፍ እንደገለጸው ከሆነ በኢሳይያስ ላይ ሞት ለማስፈረድ ሲል አንድ ሐሰተኛ ነቢይ “ኢየሩሳሌምን ሰዶም፣ የይሁዳንና የኢየሩሳሌምን አለቆች ደግሞ የገሞራ ሕዝብ ብሎ ጠርቷቸዋል” የሚል ክስ አቅርቦበታል።
-