የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • “እርቅ እንፍጠር”
    የኢሳይያስ ትንቢት—ለመላው የሰው ዘር የፈነጠቀ ብርሃን ጥራዝ 1
    • 1, 2. ይሖዋ የኢየሩሳሌምንና የይሁዳን ሕዝብ ገዥዎች ያወዳደራቸው ከማን ጋር ነው? ይህስ ተገቢ የሆነው ለምንድን ነው?

      የኢየሩሳሌም ነዋሪዎች በ⁠ኢሳይያስ 1:​1-9 ላይ ተመዝግቦ የሚገኘውን ውግዘት ከሰሙ በኋላ ለማስተባበል ይዳዳቸው ይሆናል። ለይሖዋ ያቀረቧቸውን መሥዋዕቶች ሁሉ በጉራ ለመዘርዘር እንደሚቃጣቸውም ጥርጥር የለውም። ይሁን እንጂ ከኢሳይያስ 1 ቁጥር 10 እስከ 15 ላይ ይሖዋ እንዲህ ላለው አመለካከታቸው የሚሰጠውን ኩምሽሽ የሚያደርግ መልስ እናገኛለን። እንዲህ በማለት ይጀምራል:- “እናንተ የሰዶም አለቆች ሆይ፣ የእግዚአብሔርን ቃል ስሙ፤ እናንተ የገሞራ ሕዝብ ሆይ፣ የአምላካችንን ሕግ አድምጡ።”​—⁠ኢሳይያስ 1:​10

      2 የሰዶምና ገሞራ ሰዎች የጠፉት ልቅ በሆነው የፆታ ልማዳቸው ምክንያት ብቻ ሳይሆን ልበ ደንዳናና ትዕቢተኛ ስለ ነበሩም ጭምር ነው። (ዘፍጥረት 18:​20, 21፤ 19:​4, 5, 23-25፤ ሕዝቅኤል 16:​49, 50) የኢሳይያስ አድማጮች ከእነዚያ የተረገሙ ከተሞች ሰዎች ጋር መመሳሰላቸው አስደንግጧቸው መሆን አለበት።a የሆነ ሆኖ ይሖዋ የሕዝቡን እውነተኛ ማንነት ያያል። ኢሳይያስም የእነርሱን ‘ጆሮ ለመኮርኮር’ ሲል የአምላክን መልእክት አለዝቦ አይነግራቸውም።​—⁠2 ጢሞቴዎስ 4:​3 NW

  • “እርቅ እንፍጠር”
    የኢሳይያስ ትንቢት—ለመላው የሰው ዘር የፈነጠቀ ብርሃን ጥራዝ 1
    • a የጥንቶቹ አይሁዳውያን ወግ እንደሚለው ከሆነ ክፉ የነበረው ንጉሥ ምናሴ፣ ነቢዩ ኢሳይያስ በመጋዝ ተሰንጥቆ እንዲሞት አድርጓል። (ከ⁠ዕብራውያን 11:​37 ጋር አወዳድር።) አንድ ጽሑፍ እንደገለጸው ከሆነ በኢሳይያስ ላይ ሞት ለማስፈረድ ሲል አንድ ሐሰተኛ ነቢይ “ኢየሩሳሌምን ሰዶም፣ የይሁዳንና የኢየሩሳሌምን አለቆች ደግሞ የገሞራ ሕዝብ ብሎ ጠርቷቸዋል” የሚል ክስ አቅርቦበታል።

አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
ውጣ
ግባ
  • አማርኛ
  • አጋራ
  • የግል ምርጫዎች
  • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
  • የአጠቃቀም ውል
  • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
  • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
  • JW.ORG
  • ግባ
አጋራ