-
ዓለምን የሚገዛው ማን ይሆን?የዳንኤልን ትንቢት በትኩረት ተከታተል!
-
-
ከዚያም ቂሮስ ከኃያሏ ባቢሎን ጋር ፊት ለፊት ለመጋፈጥ ተዘጋጀ። ከዚህ ጊዜ አንስቶ በመጽሐፍ ቅዱስ ትንቢት ፍጻሜ ውስጥ የበኩሉን ሚና ተጫውቷል። ይሖዋ ወደ ሁለት መቶ ከሚጠጉ ዓመታት በፊት በነቢዩ ኢሳይያስ አማካኝነት በስሙ ጠርቶ ቂሮስ የሚባል ገዥ ባቢሎንን እንደሚገለብጥና አይሁዳውያንን ከምርኮ ነፃ እንደሚያወጣ ተናግሮ ነበር። ቅዱሳን ጽሑፎችም ቂሮስ በይሖዋ ‘የተቀባ’ መሆኑን የሚናገሩት በዚህ መንገድ አስቀድሞ መሾሙን ለማመልከት ነው።—ኢሳይያስ 44:26-28
-
-
ዓለምን የሚገዛው ማን ይሆን?የዳንኤልን ትንቢት በትኩረት ተከታተል!
-
-
በባቢሎን ለነበሩት አይሁዳውያን የቂሮስ ድል ለረጅም ጊዜ ሲጠብቁት የነበረው ነፃ የሚወጡበት ጊዜ እንደደረሰና ትውልድ አገራቸው ባድማ ሆና የቆየችበት 70 ዓመት ማብቃቱን የሚያበስር ነበር። ቂሮስ ወደ ኢየሩሳሌም ተመልሰው ቤተ መቅደሱን እንደገና እንዲገነቡ የሚፈቅድ ትእዛዝ ሲያወጣ ምንኛ ተደስተው ይሆን! ከዚህም በላይ ቂሮስ፣ ናቡከደነፆር ወደ ባቢሎን አግዞት የነበረውን ውድ ንዋየ ቅድሳት የመለሰላቸው ሲሆን የግንባታ እንጨት ከሊባኖስ እንዲያስገቡ ንጉሣዊ ፈቃድ ሰጥቷቸውና የግንባታው ወጪም በንጉሡ ቤት እንዲሸፈን ፈቅዶ ነበር።—ዕዝራ 1:1-11፤ 6:3-5
-