-
ይሖዋ—‘ጻድቅ አምላክና አዳኝ’የኢሳይያስ ትንቢት—ለመላው የሰው ዘር የፈነጠቀ ብርሃን ጥራዝ 2
-
-
3. ኢሳይያስ 45:1-3 ቂሮስ የሚቀዳጀውን ድል ሥዕላዊ በሆነ መንገድ የሚገልጸው እንዴት ነው?
3 “እግዚአብሔር ለቀባሁት፣ አሕዛብንም በፊቱ አስገዛ ዘንድ የነገሥታትንም ወገብ እፈታ ዘንድ፣ በሮቹም እንዳይዘጉ መዝጊያዎቹን በፊቱ እከፍት ዘንድ፣ ቀኝ እጁን ለያዝሁት ለቂሮስ እንዲህ ይላል:- በፊትህ እሄዳለሁ ተራሮችንም ትክክል አደርጋለሁ፣ የናሱንም ደጆች እሰብራለሁ የብረቱንም መወርወሪያዎች እቈርጣለሁ፤ . . . በጨለማ የነበረችውን መዝገብ በስውርም የተደበቀችውን ሀብት እሰጥሃለሁ።”—ኢሳይያስ 45:1-3
4. (ሀ) ይሖዋ ቂሮስን ‘የቀባሁት’ ሲል የጠራው ለምንድን ነው? (ለ) ይሖዋ ቂሮስ ድል እንዲቀዳጅ የሚያደርገው እንዴት ነው?
4 ቂሮስ ኢሳይያስ በኖረበት ዘመን ገና ያልተወለደ ቢሆንም እንኳ ይሖዋ በትንቢት ልክ በሕይወት እንዳለ አድርጎ አነጋግሮታል። (ሮሜ 4:17) ይሖዋ ቂሮስን አንድ የተለየ ተልእኮ እንዲፈጽም አስቀድሞ የሾመው በመሆኑ ቂሮስ በአምላክ ‘ተቀብቷል’ ሊባል ይችላል። በአምላክ አመራር እየታገዘ ነገሥታት ምንም መከላከል እንዳይችሉ አቅማቸውን በማሽመድመድ ሕዝባቸውን በቁጥጥሩ ሥር ያደርጋል። በባቢሎን ላይ ጥቃት በሚሰነዝርበት ጊዜ ደግሞ ይሖዋ የከተማይቱ በሮች ሳይዘጉ እንዲቀሩ ስለሚያደርግ በሮቹ ልክ እንደ ተሰባበሩ መዝጊያዎች ዋጋቢስ ይሆናሉ። ይሖዋ በቂሮስ ፊት በመሄድ እንቅፋቱን ሁሉ ያስወግድለታል። በመጨረሻም የቂሮስ ወታደሮች ከተማይቱን ድል በማድረግ ጨለማ በሆኑ ግምጃ ቤቶች ውስጥ ‘በስውር የተደበቀውን ሀብት’ ይወስዳሉ። ኢሳይያስ ይህ ሁኔታ እንደሚፈጸም አስቀድሞ ተናግሯል። ታዲያ እነዚህ ቃላት ፍጻሜያቸውን አግኝተዋልን?
5, 6. በባቢሎን ላይ የሚደርሰውን ውድቀት አስመልክቶ የተነገረው ትንቢት ፍጻሜውን ያገኘው መቼና እንዴት ነው?
5 ኢሳይያስ ይህን ትንቢት ከመዘገበ ከ200 ዓመታት ገደማ በኋላ በ539 ከዘአበ ቂሮስ በባቢሎን ከተማ ላይ ጦሩን አዘመተ። (ኤርምያስ 51:11, 12) ይሁንና ባቢሎናውያን ከተማቸው በማንም ልትደፈር እንደማትችል አድርገው ያስቡ ስለነበር ሐሳባቸውን ጥለው ተቀምጠዋል። ከተማይቱ በጠላት ኃይል እንዳትደፈር ሲባል ከኤፍራጥስ ወንዝ በተጠለፈ ውኃ ዙሪያዋን ከመከበቧም በላይ በጣም ግዙፍ በሆኑ ግንቦች ታጥራለች። ከመቶ ለሚበልጡ ዓመታት ባቢሎንን በድንገት ወርሮ መቆጣጠር የቻለ አንድም የጠላት ኃይል የለም። እንዲያውም በወቅቱ ባቢሎንን በመግዛት ላይ የነበረው ብልጣሶር ምንም እንደማይደርስበት በመተማመን ከቤተ መንግሥቱ ባለሟሎች ጋር ድል ያለ ድግስ ላይ ነበር። (ዳንኤል 5:1) ያን ቀን ሌሊት ማለትም ጥቅምት 5/6 ሌሊት ቂሮስ እጅግ የረቀቀ ወታደራዊ ስልት ተጠቀመ።
6 የቂሮስ መሐንዲሶች ከባቢሎን ከተማ ውጪ የኤፍራጥስን ወንዝ አቅጣጫ በማስቀየር ወደ ከተማይቱ እንዳይፈስ አደረጉት። ብዙም ሳይቆይ ወደ ከተማይቱ ውስጥም ሆነ በከተማይቱ ዙሪያ ይፈስ የነበረው ውኃ በእጅጉ በመቀነሱ የቂሮስ ወታደሮች በወንዙ ውስጥ በመሻገር ወደ ከተማይቱ እምብርት ዘለቁ። (ኢሳይያስ 44:27፤ ኤርምያስ 50:38) የሚገርመው ነገር ኢሳይያስ አስቀድሞ በተናገረው መሠረት በወንዙ ዳርቻ ያሉት በሮች አልተዘጉም ነበር። የቂሮስ ሠራዊት ባቢሎንን በአንድ ጊዜ በመውረር ቤተ መንግሥቱን ከመቆጣጠራቸውም በላይ ንጉሥ ብልጣሶርን ገደሉት። (ዳንኤል 5:30) በአንድ ሌሊት ሁሉ ነገር አበቃ። ባቢሎን ወደቀች፤ ትንቢቱም አንድም ሳይቀር ተፈጸመ።
-
-
ይሖዋ—‘ጻድቅ አምላክና አዳኝ’የኢሳይያስ ትንቢት—ለመላው የሰው ዘር የፈነጠቀ ብርሃን ጥራዝ 2
-
-
ይሖዋ ቂሮስን የመረጠበት ምክንያት
8. ይሖዋ፣ ቂሮስ በባቢሎን ላይ ድል እንዲቀዳጅ ያደረገበት አንደኛው ምክንያት ምንድን ነው?
8 ይሖዋ ባቢሎንን ድል የሚያደርገው ማን እንደሚሆንና ከተማይቱን እንዴት እንደሚቆጣጠር ካመለከተ በኋላ ድሉን ለቂሮስ የሚሰጥበት አንደኛው ምክንያት ምን እንደሆነ ገልጿል። ትንቢታዊ በሆነ መንገድ ለቂሮስ ሲናገር “በስምህም የምጠራህ የእስራኤል አምላክ እግዚአብሔር እኔ እንደ ሆንሁ ታውቅ ዘንድ” ነው ብሎታል። (ኢሳይያስ 45:3) በመጽሐፍ ቅዱስ ታሪክ ውስጥ የተጠቀሰው አራተኛ የዓለም ኃያል መንግሥት ገዥ ታላቁን ድል የሚያቀዳጀው የእሱ የበላይ የሆነው የጽንፈ ዓለሙ ሉዓላዊ ጌታ ይሖዋ መሆኑን መገንዘቡ የተገባ ነው። ቂሮስ የጠራው ወይም ልዩ ተልእኮ የሰጠው የእስራኤል አምላክ ይሖዋ መሆኑን አምኖ መቀበል ያስፈልገው ነበር። በእርግጥም ደግሞ ቂሮስ ያን ታላቅ ድል ያቀዳጀው ይሖዋ መሆኑን አምኖ እንደተቀበለ የመጽሐፍ ቅዱስ ዘገባ ያረጋግጥልናል።—ዕዝራ 1:2, 3
-