-
ይሖዋ—‘ጻድቅ አምላክና አዳኝ’የኢሳይያስ ትንቢት—ለመላው የሰው ዘር የፈነጠቀ ብርሃን ጥራዝ 2
-
-
23. ጣዖታትን የሚያመልኩ ሰዎች መጨረሻቸው ምን ይሆናል? ይሖዋን የሚያመልኩ ሰዎችስ?
23 ይሖዋ ቀጥሎ የተናገራቸው ቃላት እስራኤላውያን የሚያገኙትን መዳን ጠበቅ አድርገው የሚገልጹ ናቸው:- “እናንተ ከአሕዛብ ወገን ሆናችሁ ያመለጣችሁ፣ ተሰብስባችሁ ኑ በአንድነትም ቅረቡ፤ የተቀረጸውን የምስላቸውን እንጨት የሚሸከሙና ያድን ዘንድ ወደማይችል አምላክ የሚጸልዩ እውቀት የላቸውም። ይናገሩ ይቅረቡም በአንድነትም ይማከሩ፤ ከጥንቱ ይህን ያሳየ ከቀድሞስ የተናገረ ማን ነው? ያሳየሁም የተናገርሁም እኔ እግዚአብሔር አይደለሁምን? ከእኔም በቀር ሌላ አምላክ የለም፤ እኔ ጻድቅ አምላክና መድኃኒት ነኝ፣ ከእኔም በቀር ማንም የለም።” (ኢሳይያስ 45:20, 21) ይሖዋ ‘ያመለጡት ሰዎች’ ያገኙትን መዳን ጣዖት የሚያመልኩት ሰዎች ከደረሰባቸው ሁኔታ ጋር እንዲያነጻጽሩ ይሰበስባቸዋል። (ዘዳግም 30:3፤ ኤርምያስ 29:14፤ 50:28) ጣዖት አምላኪዎች የሚለምኑትም ሆነ የሚያገለግሉት ሊያድኗቸው የማይችሉ ከንቱ አማልክትን ስለሆነ “እውቀት የላቸውም።” አምልኳቸው ከንቱ ነው፤ አንዳች እርባና የለውም። ይሖዋን የሚያመልኩ ሰዎች ግን በባቢሎን የሚማረኩ ሕዝቦቹን እንደሚያድን የተናገረውን ትንቢት ጨምሮ ‘ከረጅም ጊዜ በፊት’ የተነበያቸውን ነገሮች የመፈጸም ችሎታ እንዳለው ይገነዘባሉ። ይሖዋ እንዲህ ያለ ኃይልና የመተንበይ ችሎታ ያለው መሆኑ ከሌሎች አማልክት ሁሉ ልዩ ያደርገዋል። በእርግጥም ‘ጻድቅ አምላክና አዳኝ ነው።’
-
-
ይሖዋ—‘ጻድቅ አምላክና አዳኝ’የኢሳይያስ ትንቢት—ለመላው የሰው ዘር የፈነጠቀ ብርሃን ጥራዝ 2
-
-
27. ዛሬ ያሉት ክርስቲያኖች ይሖዋ የገባውን ቃል እንደሚፈጽም ሙሉ በሙሉ ሊተማመኑ የሚችሉት ለምንድን ነው?
27 እጅግ ብዙ ሰዎች ወደ አምላክ ዞር ማለታቸው ሕይወት እንደሚያስገኝላቸው እርግጠኞች መሆን የሚችሉት ለምንድን ነው? በኢሳይያስ ምዕራፍ 45 ላይ የሚገኙት ትንቢታዊ ቃላት በግልጽ እንደሚያሳዩት የይሖዋ ተስፋዎች አስተማማኝ ናቸው። ሰማያትንና ምድርን በታላቅ ጥበቡና ኃይሉ የፈጠረው ይሖዋ ትንቢቶቹ እንዲፈጸሙ ማድረግ አይሳነውም። ቂሮስን በተመለከተ የተናገረውን ትንቢት እንደፈጸመ ሁሉ ሌሎቹ የመጽሐፍ ቅዱስ ትንቢቶችም ፍጻሜያቸውን እንዲያገኙ ያደርጋል። በመሆኑም የይሖዋ አምላኪዎች በቅርቡ ይሖዋ ‘ጻድቅ አምላክና አዳኝ’ መሆኑን በድጋሚ እንደሚያረጋግጥ ሙሉ በሙሉ ሊተማመኑ ይችላሉ።
-