-
አምላክ ስለ እኛ ያስባል?እውነተኛ እምነት ደስታ ያስገኝልሃል
-
-
አምላክ ለእኛ ያለው ፍቅር እናት ለልጇ ካላት ፍቅር ይበልጣል
አምላክ ከልብ እንደሚያስብልን እርግጠኞች መሆን እንችላለን። ምክንያቱም በቅዱስ ቃሉ ውስጥ እንዲህ ብሏል፦ “እናት የምታጠባውን ልጇን ልትረሳ ትችላለች? ከማህፀኗ ለወጣውስ ልጅ አትራራም? እነዚህ ሴቶች ቢረሱ እንኳ እኔ ፈጽሞ አልረሳሽም።”a
ይህን ማወቅ አያጽናናም? የሰው ልጆች ከሚያሳዩት እጅግ ጠንካራ እንደሆኑ ከሚታሰቡ ስሜቶች አንዱ እናት ለልጇ ያላት ፍቅር ነው፤ አምላክ ለእኛ ያለው ፍቅር ከዚህ ዓይነቱ ፍቅር እንኳ የላቀ ነው። አምላክ በፍጹም አይተወንም! እንዲያውም አምላክ አስደናቂ በሆነ መንገድ እየረዳን ነው። እንዴት? ደስታ ያለው ሕይወት ለመኖር ቁልፉ ምን እንደሆነ በመጠቆም ነው፤ ይህ ቁልፍ እውነተኛ እምነት ማዳበር ነው።
-
-
አምላክ ስለ እኛ ያስባል?እውነተኛ እምነት ደስታ ያስገኝልሃል
-
-
a ቅዱስ መጽሐፉን አውጥተህ ኢሳይያስ 49:15ን ተመልከት። ቅዱስ መጽሐፉ በምዕራፎችና በቁጥሮች የተከፋፈለ ነው። ለምሳሌ ያህል፣ ኢሳይያስ 49:15 ሲባል የኢሳይያስ መጽሐፍ 49ኛው ምዕራፍ፣ ቁጥር 15 ማለት ነው።
-