-
ይሖዋ መሲሐዊ አገልጋዩን ከፍ ከፍ ያደርገዋልየኢሳይያስ ትንቢት—ለመላው የሰው ዘር የፈነጠቀ ብርሃን ጥራዝ 2
-
-
“መከራን ታግሦ ተቀበለ”
25. ኢየሱስ መከራ የተቀበለውና የሞተው በፈቃደኝነት መሆኑን እንዴት እናውቃለን?
25 መሲሑ መከራ ለመቀበልና ለመሞት ፈቃደኛ ነበርን? ኢሳይያስ እንዲህ ይላል:- “ተጨነቀ ተሣቀየም [“መከራን ታግሦ ተቀበለ፣” የ1980 ትርጉም ] አፉንም አልከፈተም፤ ለመታረድ እንደሚነዳ ጠቦት፣ በሸላቶቹም ፊት ዝም እንደሚል በግ፣ እንዲሁ አፉን አልከፈተም።” (ኢሳይያስ 53:7) ኢየሱስ ሰው ሆኖ በምድር ላይ ባሳለፈው የመጨረሻ ሌሊት “ከአሥራ ሁለት ጭፍሮች የሚበዙ መላእክት” መጥተው እንዲረዱት ማድረግ ይችል ነበር። ሆኖም “እንዲህ ከሆነስ:- እንደዚህ ሊሆን ይገባል የሚሉ መጻሕፍት እንዴት ይፈጸማሉ?” ሲል ተናግሯል። (ማቴዎስ 26:53, 54) በመሆኑም “የእግዚአብሔር በግ” ምንም ዓይነት የአጸፋ እርምጃ አልወሰደም። (ዮሐንስ 1:29) የካህናት አለቆችና ሽማግሌዎች በጲላጦስ ፊት በሐሰት ሲከሱት “ምንም አልመለሰም።” (ማቴዎስ 27:11-14) የአምላክን ፈቃድ ሊያስተጓጉል የሚችል ነገር መናገር አልፈለገም። ኢየሱስ የእሱ ሞት ታዛዥ የሆኑ የሰው ልጆችን ከኃጢአት፣ ከበሽታና ከሞት ሊቤዥ እንደሚችል በሚገባ በመገንዘቡ የመሥዋዕት በግ ሆኖ ለመሞት ፈቃደኛ ነበር።
-
-
ይሖዋ መሲሐዊ አገልጋዩን ከፍ ከፍ ያደርገዋልየኢሳይያስ ትንቢት—ለመላው የሰው ዘር የፈነጠቀ ብርሃን ጥራዝ 2
-
-
[በገጽ 206 ላይ የሚገኝ ሥዕል]
“አፉን አልከፈተም”
[ምንጭ]
በአንቶኒዮ ቺሴሪ ከተዘጋጀው “ኤከ ሆሞ” የተወሰደ
-