-
ይሖዋ ሕዝቡን በብርሃን ያስጌጣልመጠበቂያ ግንብ—2002 | ሐምሌ 1
-
-
12 እየተመሙ የሚመጡት ነጋዴዎች ብቻ አይደሉም። እረኞችም ወደ ጽዮን እየጎረፉ ነው። ትንቢቱ በመቀጠል “የቄዳር መንጎች ሁሉ ወደ አንቺ ይሰበሰባሉ የነባዮትም አውራ በጎች ያገለግሉሻል” ይላል። (ኢሳይያስ 60:7ሀ) ከብት አርቢ ነገዶችም ከመንጋቸው መካከል ለይሖዋ ምርጡን ለመስጠት ወደ ቅድስቲቱ ከተማ እየነጎዱ ነው። ከዚህም በላይ ጽዮንን ለማገልገል ራሳቸውን አቅርበዋል! ይሖዋ እነዚህን የባዕድ አገር ሰዎች የሚቀበላቸው እንዴት ይሆን? አምላክ ራሱ እንዲህ በማለት ይመልሳል:- “እኔን ደስ ሊያሰኙ በመሠዊያዬ ላይ ይወጣሉ፣ የክብሬንም ቤት አከብራለሁ [“አስጌጣለሁ፣” NW ]።” (ኢሳይያስ 60:7ለ) ይሖዋ እነዚህ የባዕድ አገር ሰዎች የሚያቀርቡትን ስጦታና አገልግሎት በአክብሮት ይቀበላል። የሚያቀርቡት ስጦታ የእሱን ቤተ መቅደስ ያስጌጣል።
-
-
ይሖዋ ሕዝቡን በብርሃን ያስጌጣልመጠበቂያ ግንብ—2002 | ሐምሌ 1
-
-
15. (ሀ) ኢሳይያስ 60:4-9 ምን ዓይነት ጭማሪ እንደሚኖር ይተነብያል? (ለ) እውነተኛ ክርስቲያኖች ምን ዓይነት መንፈስ ያሳያሉ?
15 ከ4 እስከ 9 ባሉት ቁጥሮች ላይ የሰፈረው ሐሳብ ከ1919 ወዲህ የታየውን ዓለም አቀፍ እድገት ቁልጭ አድርጎ የሚያሳይ እንዴት ያለ ሕያው ትንቢታዊ መግለጫ ነው! ይሖዋ ጽዮንን እንዲህ ባለ ጭማሪ የባረካት ለምንድን ነው? ከ1919 አንስቶ የአምላክ እስራኤል በታዛዥነትና በጽናት ብርሃኑን በማብራቱ ነው። ይሁንና ቁጥር 7 ላይ እንደተገለጸው አዲስ መጪዎቹ ‘በአምላክ መሠዊያ ላይ እንደሚወጡ’ አስተውላችኋል? መሠዊያ መሥዋዕት የሚቀርብበት ቦታ ሲሆን ይህ የትንቢቱ ገጽታ የይሖዋ አገልግሎት መሥዋዕት ማቅረብ እንደሚጠይቅ ያስታውሰናል። ሐዋርያው ጳውሎስ እንዲህ ሲል ጽፏል:- “ሰውነታችሁን እግዚአብሔርን ደስ የሚያሰኝና ሕያው ቅዱስም መሥዋዕት አድርጋችሁ ታቀርቡ ዘንድ . . . እለምናችኋለሁ፣ እርሱም ለአእምሮ የሚመች አገልግሎታችሁ ነው።” (ሮሜ 12:1) ጳውሎስ ከተናገራቸው ቃላት ጋር በሚስማማ መንገድ እውነተኛ ክርስቲያኖች በሳምንት አንዴ በሃይማኖታዊ ሥርዓቶች ላይ በመገኘታቸው ብቻ አይረኩም። ንጹሕ የሆነውን አምልኮ ለማራመድ ጊዜያቸውን፣ ጉልበታቸውንና ጥሪታቸውን ይሰጣሉ። እንዲህ ዓይነት ለአምላክ ያደሩ ሰዎች መገኘታቸው የይሖዋን ቤት የሚያስጌጥ አይደለምን? ኢሳይያስ የተናገረው ትንቢት ቤቱን እንደሚያስጌጠው ያሳያል። እንደዚህ ያሉ ቀናተኛ አምላኪዎች ደግሞ በይሖዋ ዓይን ውብ እንደሆኑ እርግጠኞች መሆን እንችላለን።
-