የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • ይሖዋ ለራሱ የከበረ ስም ያደርጋል
    የኢሳይያስ ትንቢት—ለመላው የሰው ዘር የፈነጠቀ ብርሃን ጥራዝ 2
    • 11. (ሀ) ይሖዋ ‘የበቀል ቀን’ የሚያመጣው ለምንድን ነው? (ለ) ይሖዋ በጥንት ዘመን ‘የተቤዠው’ እነማንን ነው? በዘመናችንስ?

      11 ይሖዋ ይህን ሥራ ራሱ የሚያከናውንበትን ምክንያት እንዲህ ሲል አክሎ ገልጿል:- “የምበቀልበት ቀን በልቤ ነውና፣ የምቤዥበትም ዓመት ደርሶአልና።” (ኢሳይያስ 63:4)b ሕዝቡን በሚያጠቁ ሰዎች ላይ የበቀል እርምጃ የመውሰድ መብት ያለው ይሖዋ ብቻ ነው። (ዘዳግም 32:​35) በጥንት ዘመን ይሖዋ ‘የተቤዠው’ በባቢሎናውያን እጅ ወድቀው ብዙ መከራ ያሳለፉትን አይሁዳውያን ነበር። (ኢሳይያስ 35:​10፤ 43:​1፤ 48:​20) በዘመናችን የተቤዠው ደግሞ ቅቡዓን ቀሪዎችን ነው። (ራእይ 12:​17) እንደ ጥንቶቹ የአምላክ ሕዝቦች ቅቡዓን ቀሪዎችም ከሃይማኖታዊ ግዞት ነፃ ወጥተዋል። በተጨማሪም ልክ እንደ አይሁዳውያን ቅቡዓኑም ሆኑ ‘የሌሎች በጎች’ አባላት የሆኑ አጋሮቻቸው ስደትና ተቃውሞ ሲደርስባቸው ቆይቷል። (ዮሐንስ 10:​16) በመሆኑም የኢሳይያስ ትንቢት በዛሬው ጊዜ ያሉ ክርስቲያኖች አምላክ የወሰነው ጊዜ ሲደርስ እነሱን ለመታደግ ሲል እጁን ጣልቃ አስገብቶ እርምጃ እንደሚወስድ እርግጠኞች እንዲሆኑ ዋስትና ይሰጣቸዋል።

  • ይሖዋ ለራሱ የከበረ ስም ያደርጋል
    የኢሳይያስ ትንቢት—ለመላው የሰው ዘር የፈነጠቀ ብርሃን ጥራዝ 2
    • b “የምቤዥበትም ዓመት” የሚለው አገላለጽ ይሖዋ ‘የሚበቀልበትን’ ጊዜ የሚያመለክት ሊሆን ይችላል። በ⁠ኢሳይያስ 34:​8 ላይም ከዚህ ጋር ተመሳሳይ የሆኑ መግለጫዎች እንዴት ጎን ለጎን እንደተሠራባቸው ተመልከት።

አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
ውጣ
ግባ
  • አማርኛ
  • አጋራ
  • የግል ምርጫዎች
  • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
  • የአጠቃቀም ውል
  • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
  • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
  • JW.ORG
  • ግባ
አጋራ