የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • ‘ይቅር ለማለት ዝግጁ’ የሆነ አምላክ
    ወደ ይሖዋ ቅረብ
    • በበረዶ የተሸፈኑ ተራሮች።

      “ኃጢአታችሁ . . . እንደ በረዶ ይነጣል”

      10. ይሖዋ ኃጢአታችንን ይቅር ካለን በቀሪው የሕይወት ዘመናችን ኃጢአታችን ያስከተለብንን ኀፍረት ተሸክመን እንደምንኖር ሆኖ ሊሰማን የማይገባው ለምንድን ነው?

      10 የመነቸከ ነጭ ልብስ ለማስለቀቅ ሞክረህ ታውቃለህ? የቱንም ያህል ብትፈትገው ቆሻሻው አልለቅ ይል ይሆናል። ይሁን እንጂ ይሖዋ ይቅር ባይነቱን እንዴት እንደገለጸው ልብ በል፦ “ኃጢአታችሁ እንደ ደም ቢቀላ እንደ በረዶ ይነጣል፤ እንደ ደማቅ ቀይ ጨርቅ ቢቀላም እንደ ነጭ የሱፍ ጨርቅ ይሆናል።”a (ኢሳይያስ 1:18) በራሳችን ጥረት ኃጢአታችንን ልናጠራ ወይም ልናስወግድ አንችልም። ይሁን እንጂ ይሖዋ እንደ ደም የቀላውን ወይም እንደ ደማቅ ቀይ የሆነውን ኃጢአታችንን እንደ በረዶ ወይም እንደ ነጭ የሱፍ ጨርቅ ነጭ ሊያደርገው ይችላል። ስለሆነም ይሖዋ ኃጢአታችንን አንዴ ይቅር ካለን በቀሪው የሕይወት ዘመናችን ሁሉ ኃጢአታችን ያስከተለብንን ኀፍረት ተሸክመን እንደምንኖር ሆኖ ሊሰማን አይገባም።

  • ‘ይቅር ለማለት ዝግጁ’ የሆነ አምላክ
    ወደ ይሖዋ ቅረብ
    • a አንድ ምሁር እንደገለጹት እዚህ ላይ “እንደ ደም” ተብሎ የተተረጎመው የቀለም ዓይነት “የማይለቅ ወይም የማይደበዝዝ ነው። እርጥበት፣ ዝናብ፣ እጥበት ወይም የረጅም ጊዜ አገልግሎት ሊያስለቅቀው አይችልም።”

አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
ውጣ
ግባ
  • አማርኛ
  • አጋራ
  • የግል ምርጫዎች
  • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
  • የአጠቃቀም ውል
  • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
  • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
  • JW.ORG
  • ግባ
አጋራ