የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • የሞቱ ሰዎች በምን ዓይነት ሁኔታ ላይ ይገኛሉ?
    ለዘላለም በደስታ ኑር!—አሳታፊ የመጽሐፍ ቅዱስ መማሪያ
    • 2. ስለ ሞት እውነቱን ማወቃችን ምን ጥቅም ያስገኝልናል?

      ብዙ ሰዎች ሞትን አልፎ ተርፎም የሞቱ ሰዎችን ይፈራሉ! መጽሐፍ ቅዱስ ስለ ሞት የሚናገረውን ነገር ማወቅ ግን ያጽናናል። ኢየሱስ ‘እውነት ነፃ ያወጣችኋል’ ብሏል። (ዮሐንስ 8:32) አንዳንድ ሃይማኖቶች ሰው ከሞተ በኋላ በሕይወት መኖሯን የምትቀጥል የማትሞት ነፍስ እንዳለች ያስተምራሉ፤ መጽሐፍ ቅዱስ ግን እንዲህ አይልም። ማንም ሰው ከሞተ በኋላ አይሠቃይም። በተጨማሪም ሙታን ምንም ነገር ስለማያውቁ እኛን ሊጎዱን አይችሉም። እንዲሁም ከሞቱ ሰዎች ጋር በተያያዘ ለየት ያለ ሃይማኖታዊ ሥርዓት መፈጸም ወይም ስለ እነሱ መጸለይ አያስፈልገንም።

      አንዳንዶች ‘የሞቱ ሰዎችን ማነጋገር እንችላለን’ ይላሉ። ሆኖም ይህ ሊሆን የማይችል ነገር ነው። ቀደም ሲል እንደተመለከትነው ‘ሙታን ምንም አያውቁም።’ በሞት የተለዩአቸውን ሰዎች እንደሚያነጋግሩ የሚያስቡ ሰዎች የሚያነጋግሩት የሞቱትን ሰዎች ሳይሆን እነሱን መስለው የሚቀርቡ አጋንንትን ሊሆን ይችላል። ስለዚህ ሞትን በተመለከተ እውነቱን ማወቃችን ከአጋንንት ይጠብቀናል። ይሖዋ ከሞቱ ሰዎች ጋር ለመነጋገር መሞከር እንደሌለብን አስጠንቅቆናል፤ ምክንያቱም አጋንንት በዚህ ተጠቅመው ሊጎዱን እንደሚችሉ ያውቃል።—ዘዳግም 18:10-12⁠ን አንብብ።

  • የሞቱ ሰዎች በምን ዓይነት ሁኔታ ላይ ይገኛሉ?
    ለዘላለም በደስታ ኑር!—አሳታፊ የመጽሐፍ ቅዱስ መማሪያ
    • 4. ስለ ሞት እውነቱን ማወቃችን ይጠቅመናል

      ሞትን በተመለከተ እውነቱን ማወቃችን የሞቱ ሰዎችን እንዳንፈራ ይረዳናል። መክብብ 9:10⁠ን አንብቡ፤ ከዚያም በሚከተለው ጥያቄ ላይ ተወያዩ፦

      • የሞቱ ሰዎች ሊጎዱን ይችላሉ?

      የመጽሐፍ ቅዱስን እውነት ማወቃችን ‘የሞቱ ሰዎች በሕይወት ያሉትን ሊጎዱ ይችላሉ’ ወይም ‘ሊመለኩ ይገባል’ ከሚለው እምነትም ይጠብቀናል። ኢሳይያስ 8:19⁠ን እና ራእይ 4:11⁠ን አንብቡ፤ ከዚያም በሚከተለው ጥያቄ ላይ ተወያዩ፦

      • ለሞቱ ሰዎች አምልኮ የሚያቀርብን ወይም የእነሱን እርዳታ ለማግኘት የሚሞክርን ሰው በተመለከተ ይሖዋ ምን የሚሰማው ይመስልሃል?

      የሞቱ ሰዎችን ለማክበር ተብለው የሚደረጉ ልማዶችን የሚያሳዩ ሥዕሎች፦ 1. አንድ ሰው የመቃብር ቦታ ጋ ምግብ አቅርቦ ተንበርክኮ ሲጸልይ 2. ሦስት ሰዎች ለየት ያለ ልብስ ለብሰው ሲጨፍሩ 3. ከራስ ቅል የተሠሩ ጭንብሎች አድርገው እንዲሁም ትላልቅ አጽሞችን ይዘው ሰልፍ የወጡ ሰዎች

      ስለ ሞት እውነቱን ማወቃችን ይሖዋን ከሚያሳዝኑ ልማዶች እንድንርቅ ይረዳናል

አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
ውጣ
ግባ
  • አማርኛ
  • አጋራ
  • የግል ምርጫዎች
  • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
  • የአጠቃቀም ውል
  • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
  • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
  • JW.ORG
  • ግባ
አጋራ