የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • በመሲሑ ግዛት የሚገኝ መዳንና ደስታ
    የኢሳይያስ ትንቢት—ለመላው የሰው ዘር የፈነጠቀ ብርሃን ጥራዝ 1
    • 4, 5. ኢሳይያስ የመሲሑን መምጣት በተመለከተ ምን ትንቢት ተናግሯል? ማቴዎስ ጠቅሶ የተናገረው የትኞቹን የኢሳይያስ ቃላት ነው?

      4 ከኢሳይያስ ዘመን ብዙ መቶ ዓመታት ቀደም ብሎ ሌሎች ዕብራውያን የመጽሐፍ ቅዱስ ጸሐፊዎችም ስለ መሲሑ ማለትም ይሖዋ ወደ እስራኤል ስለሚልከው እውነተኛ መሪ መምጣት ተናግረው ነበር። (ዘፍጥረት 49:​10፤ ዘዳግም 18:​18፤ መዝሙር 118:​22, 26) አሁን ደግሞ ይሖዋ በኢሳይያስ አማካኝነት ተጨማሪ ዝርዝር ጉዳዮችን ይገልጻል። ኢሳይያስ እንዲህ ሲል ጽፏል:- “ከእሴይ ግንድ በትር ይወጣል፣ ከሥሩም ቁጥቋጥ ያፈራል። ” (ኢሳይያስ 11:​1፤ ከ⁠መዝሙር 132:​11 ጋር አወዳድር።) “በትር” እና “ቁጥቋጥ” የሚሉት ሁለቱም መግለጫዎች መሲሑ የእስራኤል ንጉሥ ሆኖ በዘይት በተቀባው በእሴይ ልጅ በዳዊት በኩል የሚመጣ የእሴይ ዘር እንደሆነ የሚያመለክቱ ናቸው። (1 ሳሙኤል 16:​13፤ ኤርምያስ 23:​5፤ ራእይ 22:​16) እውነተኛው መሲሕ ማለትም ከዳዊት ቤት የሚወጣው ይህ “ቁጥቋጥ” ሲመጣ መልካም ፍሬዎችን ያፈራል።

      5 ተስፋ የተሰጠበት መሲሕ ኢየሱስ ነው። የወንጌል ጸሐፊ የሆነው ማቴዎስ ኢየሱስ “ናዝራዊ” ተብሎ መጠራቱ የነቢያት ቃል ፍጻሜ ነው ብሎ ሲጽፍ በተዘዋዋሪ መንገድ ኢሳይያስ 11:​1ን መጥቀሱ ነበር። ኢየሱስ ያደገው በናዝሬት ከተማ በመሆኑ ናዝራዊ ተብሎ ተጠርቷል። ይህ ስም በ⁠ኢሳይያስ 11:​1 ላይ ከተጠቀሰው “ቁጥቋጥ” የሚል ትርጉም ካለው የዕብራይስጥ ቃል ጋር የሚዛመድ ነው።b​—⁠ማቴዎስ 2:​23፣ የአዲሲቱ ዓለም ትርጉም የግርጌ ማስታወሻ፤ ሉቃስ 2:​39, 40

  • በመሲሑ ግዛት የሚገኝ መዳንና ደስታ
    የኢሳይያስ ትንቢት—ለመላው የሰው ዘር የፈነጠቀ ብርሃን ጥራዝ 1
    • b “ቁጥቋጥ” የሚለው የዕብራይስጥ ቃል ኔሰር ሲሆን “ናዝራዊ” የሚለው ደግሞ ኖስሪ ነው

አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
ውጣ
ግባ
  • አማርኛ
  • አጋራ
  • የግል ምርጫዎች
  • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
  • የአጠቃቀም ውል
  • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
  • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
  • JW.ORG
  • ግባ
አጋራ