-
ይሖዋ ኩሩዋን ከተማ ያዋርዳልየኢሳይያስ ትንቢት—ለመላው የሰው ዘር የፈነጠቀ ብርሃን ጥራዝ 1
-
-
10. ባቢሎንን ድል ለማድረግ ይሖዋ የሚጠቀመው በማን ነው?
10 ይሖዋ ባቢሎንን ለመጣል የሚጠቀምበት ኃይል የትኛው ይሆን? ከ200 ዓመታት ቀደም ብሎ ይሖዋ መልሱን ሰጥቷል:- “እነሆ፣ ብር የማይሹትን፣ ወርቅም የማያምራቸውን ሜዶናውያንን በላያቸው አስነሣለሁ። ፍላጾቻቸውም ጎበዞችን ይጨፈጭፋሉ፣ የማኅፀንንም ፍሬ አይምሩም፣ ዓይኖቻቸውም ለሕፃናት አይራሩም። እግዚአብሔርም ሰዶምንና ገሞራን ባፈረሰ ጊዜ እንደ ነበረው፣ የመንግሥታት ክብር የከለዳውያንም ትዕቢት ጌጥ ባቢሎን እንዲሁ ትሆናለች።” (ኢሳይያስ 13:17-19) የተቀማጠለችው ባቢሎን ትወድቃለች። ለይሖዋ እንደ መሣሪያ ሆኖ ይህን የሚያስፈጽመው ደግሞ በሩቅ ካለው የሜዶን ተራራማ አካባቢ የሚመጣ ሠራዊት ይሆናል።a በመጨረሻም ባቢሎን በሥነ ምግባር ብልግና የለየላቸው እንደነበሩት እንደ ሰዶምና ገሞራ ከተሞች ባድማ ትሆናለች።—ዘፍጥረት 13:13፤ 19:13, 24
-
-
ይሖዋ ኩሩዋን ከተማ ያዋርዳልየኢሳይያስ ትንቢት—ለመላው የሰው ዘር የፈነጠቀ ብርሃን ጥራዝ 1
-
-
13, 14. (ሀ) የሜዶንና የፋርስ ተዋጊዎች ለምርኮ እምብዛም ባይጎመጁም ከፍተኛ ግምት የሚሰጡት ለምን ነገር ነበር? (ለ) ቂሮስ ባቢሎን ትኩራራበት የነበረውን መከላከያ ያለፈው እንዴት ነው?
13 የሜዶንም ሆኑ የፋርስ ተዋጊዎች ለምርኮ ያላቸው ፍቅር እምብዛም ይሁን እንጂ የሥልጣን ጥም ግን ነበራቸው። በዓለም መድረክ ከየትኛውም መንግሥት አንሰው መገኘት አይፈልጉም። ከዚህም በላይ ይሖዋ በልባቸው ‘ጥፋትን’ አስገብቷል። (ኢሳይያስ 13:6) በመሆኑም የባቢሎናውያን እናቶች የማኅፀን ፍሬ የሆኑትን የጠላት ወታደሮች ‘የሚጨፈጭፉበትን’ ፍላጻ ለማስወንጨፍ በሚጠቀሙበት ጠንካራ ደጋን አማካኝነት ባቢሎንን ለማንበርከክ ቆርጠዋል።
-