-
ይሖዋን በመተማመን ተጠባበቁየኢሳይያስ ትንቢት—ለመላው የሰው ዘር የፈነጠቀ ብርሃን ጥራዝ 1
-
-
22. የታመኑት ሰዎች ከሚያገኙት በረከት በተቃራኒ ይሖዋ ለክፉዎች ምን አዘጋጅቶላቸዋል?
22 ኢሳይያስ መልእክቱን የሚናገርበት የድምፅ ቃና እንደገና ይቀየራል። የአድማጮቹን ትኩረት ማግኘት የፈለገ ይመስል“እነሆ” በማለት ይጀምራል። “የእግዚአብሔር ስም ከሚነድድ ቁጣ ከሚትጐለጐልም ጢስ ጋር ከሩቅ ይመጣል፤ ከንፈሮቹም ቁጣን የሞሉ ናቸው፣ ምላሱም እንደምትበላ እሳት ናት።” (ኢሳይያስ 30:27) እስከዚህ ጊዜ ድረስ ይሖዋ የሕዝቡ ጠላቶች የራሳቸውን ጎዳና ሲከተሉ እጁን ጣልቃ ሳያስገባ ቆይቷል። አሁን ግን ወደፊት እንደሚገሰግስ ወዠብ ፍርዱን ለማስፈጸም ወደ እነርሱ እየተጠጋ ነው። “እስትንፋሱም አሕዛብን በአጥፊ ወንፊት ሊነፋቸው እንደሚያጥለቀልቅ እስከ አንገትም እንደሚደርስ ወንዝ ነው፣ በሕዝብም መንጋጋ የሚያስት ልጓም ይሆናል።” (ኢሳይያስ 30:28) የአምላክ ሕዝብ ጠላቶች ‘በሚያጥለቀልቅ ወንዝ’ ተከብበው ‘በወንፊት እንደሚነፉ’ ያህል ይወዘወዛሉ እንዲሁም ‘በልጓም’ ይጎተታሉ። አዎን፣ ይጠፋሉ።
-
-
ይሖዋን በመተማመን ተጠባበቁየኢሳይያስ ትንቢት—ለመላው የሰው ዘር የፈነጠቀ ብርሃን ጥራዝ 1
-
-
[በገጽ 312 ላይ የሚገኝ ሥዕል]
ይሖዋ “ከሚነድድ ቁጣ ከሚትጎለጎልም ጢስ ጋር” ይመጣል
-